ከአዋሽ ይቀበሉ ያሸንፉ በሚል መሪ ቃል ከነሐሴ 21 ቀን 2010 እስክ ሕዳር 20 ቀን 2011 ዓ.ም ሲካሄድ የነበረው የውጭ ምንዛሪ ሎተሪ መርሃ-ግብር ታሕሳስ 9 ቀን 2011 ዓ.ም በኢትየጵያ ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር አዳራሽ በተካሄደ የዕጣ አወጣጥ ሥነ-ሥርዓት ላይ አሸናፊ ባለዕደለኞች ተለይቷል፡፡ በዚሁ መሠረት የአንደኛው ዕጣ አሸናፊ የሆኑትና የአይሱዚ የጭነት መኪና ተሸላሚ አቶ ሃሰን አባገሮ አባጊሳ የመኪናውን ቁልፍ ከባንኩ ከፍተኛ የስራ አመራሮች ተቀብለዋል ፡፡ እንዲሁም በአዲስ አበባ የሚገኙ የሁለተኛ እና የሶስተኛ ዕጣ አሸናፊዎች የተዘጋጀላቸውን ቴሌቪዥን እና የውሃ ማጣሪያ ማሽኖች ተረክበዋል፡፡