አዋሽ ባንክ ከዘጠኝ አነስተኛ ፋይናንስ ተቋማት ጋር የብድር አቅርቦት ስምምነት አደረገ

አዋሽ ባንክ መካከለኛ፣ አነስተኛና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያገኙ ከዘጠኝ አነስተኛ ፋይናንስ ተቋማት ጋር የብድር አቅርቦት ስምምነት አድርጓል፡፡ ባንኩ ይህን ስምምነት ያደረገው ዘጠኙ አነስተኛ ፋይናንስ ተቋማትም፦ ቪዥን ፈንድ፣ ንስር፣ ቀንዲል፣ መተማመን፣ መክሊት፣ ዳይናሚክ፣ ዋሳሳ፣ ሃርቡ እና ፒስ አነስተኛ ፋይናንስ ተቋም ይገኙበታል።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የስራና ክህሎት ምኒስቴር ምኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈርሃት ካሚል እንደተናገሩት የመካከለኛ፣ አነስተኛና ጥቃቅን የሥራ ዘርፎች ለሥራ ዕድል ፈጠራ ፣ ለኢኮኖሚ ዕድገት እና ለማህበራዊ ችግሮች ማቃለያ ከፍተኛ ሚና ቢኖራቸውም ያላቸውን እምቅ አቅም ተጠቅመው ወደ ሥራ ለመግባት የፋይናንስ አቅርቦት ውስንነት እንዳለባቸው በመግለፅ ባንኩ ላደረገው የብድር ድጋፍ ምስጋናቸውን ያቀረቡ ሲሆን ሌሎች የፋይናንስ ተቋማትም ለዘርፉ እድገት አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Mar 28, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.6139 57.7462
GBP
68.2965 69.6624
EUR
61.3298 62.5564
AED
13.9500 14.2290
SAR
13.6595 13.9327
CHF
59.6955 60.8894

Exchange Rate
Close