የአዋሽ ባንክ የባለአክሲዮኖች 26ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ህዳር 18 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሒልተን ሆቴል ተካሄደ፡፡

የአዋሽ ባንክ የባለአክሲዮኖች 26ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ህዳር 18 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሒልተን ሆቴል ተካሂዷል፡፡ በስብሰባውም ላይ የአዋሽ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አምባሳደር ዶ/ር ዲባባ አብደታ በተጠናቀቀው የ2020/21 የሂሣብ ዓመት አዋሽ ባንክ በሁሉም የሥራ ዘርፎች አመርቂ ውጤቶችን ማስመዝገቡንና ከግል ባንኮች የመሪነት ሥፍራውን ለተከታታይ ዓመታት ይዞ መቀጠሉን አስረድተዋል፡፡ በባንኩም የ10 ዓመት ፍኖተ ካርታ መሠረት እ.ኤ.አ. 2025 መጨረሻ ላይ ከአሥር ምርጥ የምሥራቅ አፍሪካ ባንኮች መካከል አንዱ ለመሆን ያስቀመጠውን ግብ በተሳካ ሁኔታ እያሳካ መሆኑን የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢው ገልጸዋል፡፡
ባንኩ ይህንን አመርቂ ውጤት ማስመዝገብ የቻለው በዓለም አቀፍ እና በአገር አቀፍ ደረጃ የተደቀኑበትን ፈተናዎች ሁሉ ተቋቁሞ ስለሆነ ለዚህ ውጤት ያበቁትን አካላት ማለትም የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላትን፣ የሥራ አመራር አባላትንና ሠራተኞችን፣ ባለአክሲዮኖችን፣ ደንበኞችን፣ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑትን አካላት ሁሉ አመስግነዋል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Apr 25, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.8795 58.0171
GBP
67.5577 68.9089
EUR
60.7928 62.0087
AED
14.0132 14.2935
SAR
13.7240 13.9985
CHF
59.3920 60.5798

Exchange Rate
Close