አዋሽ ባንክ የካናዳ ክርስቲያን ህፃናት ፈንድ ከተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር በአዳማ ከተማ ከኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል ለተፈናቀሉ ህፃናት የተሟላ የመጠጥ ውሃና ዘመናዊ መጸዳጃ ቤቶች እንዲሁም የህፃናት መጫወቻዎች ያሏቸው የመማሪያ ክፍሎችን አስገነባ፡፡

የኮርፖሬት ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት የሚታወቀው አዋሽ ባንክ ባለፈው ዓመት 25ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ባከበረበት ወቅት ለተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች በሚሊዮኖች የሚቆጠር የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ የብር አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ የገንዘብ ድጋፍ ያገኘው የካናዳ የክርስቲያን ህፃናት ፈንድ የተሰኘ ዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅት ነው፡፡ ድርጅቱም ከባንኩ ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ ከኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል ለተፈናቀሉ ህፃናት መማሪያ የሚውል የመማሪያ ክፍሎችን ከዘመናዊ መፀዳጃ ቤቶች፣ ከህፃናት መጫወቻዎችና ከመጠጥ ውሃ ጋር በመገንባት ለህብረተሰቡ ያስረከበ ሲሆን ብሎኩንም በአዋሽ ባንክ ስም ሰይሟል፡፡ ትምህርት ቤቱም በመጪው ሐሙስ የካቲት 18 ቀን 2013 ዓ.ም የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኃላፊዎች በተገኙበት በይፋ ይመረቃል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Apr 25, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.8795 58.0171
GBP
67.5577 68.9089
EUR
60.7928 62.0087
AED
14.0132 14.2935
SAR
13.7240 13.9985
CHF
59.3920 60.5798

Exchange Rate
Close