አዋሽ ባንክ እና የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።

አዋሽ ባንክ በሃገራችን እየተስፋፋ የመጣውንና በተለይ ባንኮችን ተጋላጭ የሚያደርገውን በውክልና ሰነዶች የማጭበርበር ወንጀል ለመከላከል የሚያስችለውን የመግባቢያ ሰነድ ከፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ ጋር ነሃሴ 24 ቀን 2013 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል ተፈራርሟል። የመግባቢያ ሰነዱን የፈረሙት የአዋሽ ባንክ ሆል ሴል ባንኪንግ ቺፍ ኦፊሰር አቶ ታደሰ ገመዳ እና የፌዴራል የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን አማረ ናቸው፡፡
ስምምነቱ በተለይም የዉክልና ሰነዶችን ትክክለኛነትና ህጋዊነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል በመሆኑ ከፍተኛ የማጭበርበር ወንጀሎችን ለማስቀረት የሚያስችል መሆኑን የመግባቢያ ስምምነቱን የተፈራረሙት የኤጀንሲዉ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን አማረና የአዋሽ ባንክ ሆል ሴል ባንኪንግ ቺፍ ኦፊሰር አቶ ታደሰ ገመዳ ገልፀዋል። ስምምነቱ ቀደም ሲል በዉክልና የሚንቀሳቀሱ የባንክ ሂሳቦችንና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ የዉክልናዉን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ በባንክ ባለሙያዎች ወደ ኤጀንሲዉ ይደወል የነበረዉን በማስቀረት ኦንላይን ለማረጋገጥ ስለሚያስችል ቀደም ሲል የነበረዉን እንግልትና የተንዛዛ አሰራር ሙሉ በመሉ የሚያስቀር ነዉ ተብሏል።

 

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Feb 05, 2025 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
124.7041 127.1982
GBP
153.3074 156.3735
EUR
135.2163 137.9206
JPY
0.7393 0.7541
SAR
30.0824 30.6840
AED
30.7258 31.3403
CAD
81.5563 83.1874
CHF
135.5787 138.2903
NOK
10.1355 10.3382
DKK
16.4011 16.7291