አዋሽ ባንክ የካናዳ ክርስቲያን ህፃናት ፈንድ ከተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር በአዳማ ከተማ ከኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል ለተፈናቀሉ ህፃናት የተሟላ የመጠጥ ውሃና ዘመናዊ መጸዳጃ ቤቶች እንዲሁም የህፃናት መጫወቻዎች ያሏቸው የመማሪያ ክፍሎችን አስገነባ፡፡

የኮርፖሬት ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት የሚታወቀው አዋሽ ባንክ ባለፈው ዓመት 25ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ባከበረበት ወቅት ለተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች በሚሊዮኖች የሚቆጠር የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ የብር አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ የገንዘብ ድጋፍ ያገኘው የካናዳ የክርስቲያን ህፃናት ፈንድ የተሰኘ ዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅት ነው፡፡ ድርጅቱም ከባንኩ ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ ከኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል ለተፈናቀሉ ህፃናት መማሪያ የሚውል የመማሪያ ክፍሎችን ከዘመናዊ መፀዳጃ ቤቶች፣ ከህፃናት መጫወቻዎችና ከመጠጥ ውሃ ጋር በመገንባት ለህብረተሰቡ ያስረከበ ሲሆን ብሎኩንም በአዋሽ ባንክ ስም ሰይሟል፡፡ ትምህርት ቤቱም በመጪው ሐሙስ የካቲት 18 ቀን 2013 ዓ.ም የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኃላፊዎች በተገኙበት በይፋ ይመረቃል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Sep 29, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
55.2224 56.3268
GBP
64.2394 65.5242
EUR
58.5247 59.6952
AED
13.6041 13.8762
SAR
13.3217 13.5881
CHF
57.7817 58.9373

Exchange Rate
Close