አዋሽ ባንክ የካናዳ ክርስቲያን ህፃናት ፈንድ ከተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር በአዳማ ከተማ ከኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል ለተፈናቀሉ ህፃናት የተሟላ የመጠጥ ውሃና ዘመናዊ መጸዳጃ ቤቶች እንዲሁም የህፃናት መጫወቻዎች ያሏቸው የመማሪያ ክፍሎችን አስገነባ፡፡

የኮርፖሬት ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት የሚታወቀው አዋሽ ባንክ ባለፈው ዓመት 25ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ባከበረበት ወቅት ለተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች በሚሊዮኖች የሚቆጠር የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ የብር አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ የገንዘብ ድጋፍ ያገኘው የካናዳ የክርስቲያን ህፃናት ፈንድ የተሰኘ ዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅት ነው፡፡ ድርጅቱም ከባንኩ ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ ከኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል ለተፈናቀሉ ህፃናት መማሪያ የሚውል የመማሪያ ክፍሎችን ከዘመናዊ መፀዳጃ ቤቶች፣ ከህፃናት መጫወቻዎችና ከመጠጥ ውሃ ጋር በመገንባት ለህብረተሰቡ ያስረከበ ሲሆን ብሎኩንም በአዋሽ ባንክ ስም ሰይሟል፡፡ ትምህርት ቤቱም በመጪው ሐሙስ የካቲት 18 ቀን 2013 ዓ.ም የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኃላፊዎች በተገኙበት በይፋ ይመረቃል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Jul 26, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
57.4895 58.6393
GBP
70.6759 72.0894
EUR
62.3359 63.5826
AED
14.1646 14.4479
SAR
13.8682 14.1456
CHF
62.5028 63.7529

Exchange Rate
Close