አዋሽ ባንክ የካናዳ ክርስቲያን ህፃናት ፈንድ ከተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር በአዳማ ከተማ ከኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል ለተፈናቀሉ ህፃናት የተሟላ የመጠጥ ውሃና ዘመናዊ መጸዳጃ ቤቶች እንዲሁም የህፃናት መጫወቻዎች ያሏቸው የመማሪያ ክፍሎችን አስገነባ፡፡

የኮርፖሬት ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት የሚታወቀው አዋሽ ባንክ ባለፈው ዓመት 25ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ባከበረበት ወቅት ለተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች በሚሊዮኖች የሚቆጠር የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ የብር አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ የገንዘብ ድጋፍ ያገኘው የካናዳ የክርስቲያን ህፃናት ፈንድ የተሰኘ ዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅት ነው፡፡ ድርጅቱም ከባንኩ ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ ከኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል ለተፈናቀሉ ህፃናት መማሪያ የሚውል የመማሪያ ክፍሎችን ከዘመናዊ መፀዳጃ ቤቶች፣ ከህፃናት መጫወቻዎችና ከመጠጥ ውሃ ጋር በመገንባት ለህብረተሰቡ ያስረከበ ሲሆን ብሎኩንም በአዋሽ ባንክ ስም ሰይሟል፡፡ ትምህርት ቤቱም በመጪው ሐሙስ የካቲት 18 ቀን 2013 ዓ.ም የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኃላፊዎች በተገኙበት በይፋ ይመረቃል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Mar 09, 2026 - EXCHANGE Rate
CurrencyCash and Remittances through AgentsTransaction
BuyingSellingBuyingSelling
USD USD153.2439156.3088153.0141156.0744
GBP GBP207.4951211.6450207.4951211.6450
EUR EUR181.4794185.1090181.4794185.1090
JPY JPY1.01121.03141.01631.0366
SAR SAR43.084043.945743.587744.4595
AED AED44.022344.902744.539545.4303
CAD CAD111.3935113.6214112.6983114.9523
CHF CHF195.6127199.5250197.8906201.8484
NOK NOK14.737615.032413.697013.9709
DKK DKK23.213723.678023.485123.9548
SEK SEK17.027717.368317.226817.5713