አዋሽ ባንክ የካቲት 27 ቀን 2012 ዓ.ም ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ብቻ የሚሰጥ ቅርንጫፍ በደቡብ ብሔሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት፣ በሐላባ ከተማ ‘አማና’ ተብሎ የተሰየመውን የተሟላ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጥ ቅርንጫፍ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት አድረጓል፡፡

በመላው የአገሪቱ ክፍሎች ለደንበኞቹ ቀልጣፋ፣ የተሟላና ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት በመስጠት የሚታወቀው ባንካችን አገልግሎቱን በተሻለ ደረጃ ለመስጠት የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ ሲሆን እስከ ዛሬ ድረስ በሁሉም ቅርንጫፎች በመስኮት ደረጃ ይሰጥ የነበረውን ከወለድ ነፃ የባንክ አገልገሎትን አሁን ደግሞ ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጡ ቅርንጫፎችን በመክፈት ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ መሠረት ይህን ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ኢክኽላስ ብሎ በመሰየም (ብራንድ በማድረግ) እንቅስቃሴ የጀመረ ሲሆን በአጭር ጊዜ ውስጥ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጡ በአዲስ አበባ ከተማ አራት ቅርንጫፎች፣ በምስራቅ ሐረርጌ ዞን መልካ ራፉ ከተማ፣ በጅግጅጋ እና በጅማ ከተማ በመክፈት የተሟላ የባንክ አገለግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Nov 28, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
55.6854 56.7991
GBP
67.1870 68.5307
EUR
60.9588 62.1780
AED
13.7216 13.9960
SAR
13.4363 13.7050
CHF
60.3764 61.5839

Exchange Rate
Close