አዋሽ ባንክ የካቲት 27 ቀን 2012 ዓ.ም ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ብቻ የሚሰጥ ቅርንጫፍ በደቡብ ብሔሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት፣ በሐላባ ከተማ ‘አማና’ ተብሎ የተሰየመውን የተሟላ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጥ ቅርንጫፍ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት አድረጓል፡፡

በመላው የአገሪቱ ክፍሎች ለደንበኞቹ ቀልጣፋ፣ የተሟላና ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት በመስጠት የሚታወቀው ባንካችን አገልግሎቱን በተሻለ ደረጃ ለመስጠት የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ ሲሆን እስከ ዛሬ ድረስ በሁሉም ቅርንጫፎች በመስኮት ደረጃ ይሰጥ የነበረውን ከወለድ ነፃ የባንክ አገልገሎትን አሁን ደግሞ ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጡ ቅርንጫፎችን በመክፈት ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ መሠረት ይህን ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ኢክኽላስ ብሎ በመሰየም (ብራንድ በማድረግ) እንቅስቃሴ የጀመረ ሲሆን በአጭር ጊዜ ውስጥ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጡ በአዲስ አበባ ከተማ አራት ቅርንጫፎች፣ በምስራቅ ሐረርጌ ዞን መልካ ራፉ ከተማ፣ በጅግጅጋ እና በጅማ ከተማ በመክፈት የተሟላ የባንክ አገለግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

May 31, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
54.3041 55.3902
GBP
64.4469 65.7358
EUR
58.2683 59.4337
AED
13.3787 13.6463
SAR
13.1039 13.3660
CHF
57.4567 58.6058

Exchange Rate
Close