አዋሽ ባንክ የካቲት 12 ቀን 2012 ዓ.ም የደቡብ ምዕራብ የአገራችን ክፍል ፈርጥ በሆነችውና በንግድ መዳረሻነቷ በምትታወቀው ጥንታዊቷ የጅማ ከተማ ‘ሂራ’ ተብሎ የተሰየመውን የተሟላ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጥ ቅርንጫፍ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት አድረጓል፡

በመላው የአገሪቱ ክፍሎች ለደንበኞቹ ቀልጣፋ፣ የተሟላና ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት በመስጠት የሚታወቀው ባንካችን አገልግሎቱን በተሻለ ደረጃ ለመስጠት የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ ሲሆን እስከ ዛሬ ድረስ በሁሉም ቅርንጫፎች በመስኮት ደረጃ ይሰጥ የነበረውን ከወለድ ነፃ የባንክ አገልገሎትን አሁን ደግሞ ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጡ ቅርንጫፎችን በመክፈት ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ መሠረት ይህን ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ኢክኽላስ ብሎ በመሰየም (ብራንድ በማድረግ) እንቅስቃሴ የጀመረ ሲሆን በአጭር ጊዜ ውስጥ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጡ አራት ቅርንጫፎችን በአዲስ አበባ ከተማ በመክፈት የተሟላ የባንክ አገለግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ እንደዚሁም በምስራቁ የአገራችን ክፍልም በምስራቅ ሐረርጌ ዞን መልካ ራፉ ከተማ እና በኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጡ ቅርንጫፎችን ከፍቶ ለአገልገሎት አብቅቷል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Sep 29, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
55.2224 56.3268
GBP
64.2394 65.5242
EUR
58.5247 59.6952
AED
13.6041 13.8762
SAR
13.3217 13.5881
CHF
57.7817 58.9373

Exchange Rate
Close