አዋሽ ባንክ የካቲት 12 ቀን 2012 ዓ.ም የደቡብ ምዕራብ የአገራችን ክፍል ፈርጥ በሆነችውና በንግድ መዳረሻነቷ በምትታወቀው ጥንታዊቷ የጅማ ከተማ ‘ሂራ’ ተብሎ የተሰየመውን የተሟላ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጥ ቅርንጫፍ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት አድረጓል፡

በመላው የአገሪቱ ክፍሎች ለደንበኞቹ ቀልጣፋ፣ የተሟላና ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት በመስጠት የሚታወቀው ባንካችን አገልግሎቱን በተሻለ ደረጃ ለመስጠት የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ ሲሆን እስከ ዛሬ ድረስ በሁሉም ቅርንጫፎች በመስኮት ደረጃ ይሰጥ የነበረውን ከወለድ ነፃ የባንክ አገልገሎትን አሁን ደግሞ ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጡ ቅርንጫፎችን በመክፈት ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ መሠረት ይህን ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ኢክኽላስ ብሎ በመሰየም (ብራንድ በማድረግ) እንቅስቃሴ የጀመረ ሲሆን በአጭር ጊዜ ውስጥ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጡ አራት ቅርንጫፎችን በአዲስ አበባ ከተማ በመክፈት የተሟላ የባንክ አገለግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ እንደዚሁም በምስራቁ የአገራችን ክፍልም በምስራቅ ሐረርጌ ዞን መልካ ራፉ ከተማ እና በኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጡ ቅርንጫፎችን ከፍቶ ለአገልገሎት አብቅቷል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Sep 07, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
115.1001 118.7426
GBP
141.5006 145.9786
EUR
124.8029 128.7525
AED
28.3594 29.2569
SAR
27.7656 28.6444
CHF
125.1372 129.0973

Exchange Rate
Close