አዋሽ ባንክ የመጋዘን ደረሰኝ የብድር አገልግሎት መስጠት ጀመረ!

የመጋዘን ደረሰኝ ብድር አንድ አምራች ወይም ተገበያይ ምርቱን ወደ ኢትዮጵያ ምርት ገበያ መጋዘን በማስገባትና የመጋዘን ደረሰኙን (WR) እንደ ማስያዣ በመጠቀም ከምርት ገበያው ጋር በጣምራ ከሚሰሩ ባንኮች ብድር አገልግሎት የሚያገኝበት አሰራር ነው፡፡በዚህ መሰረት ተበዳሪው አርሶ አደር፣ የህብረት ስራ ማህበራት ዩኒየኖች እና አቅራቢዎች መያዣ እንዲሆን ካስገባው ምርት ውጭ ሌላ ንብረት ለመያዣነት ሳያስፈልገው ከባንክ የአጭር ጊዜ የብድር አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ፡፡
በዚሁ መሰረት አዋሽ ባንክ ከኢትዮጵያ የምርት ገበያ ድርጅት ጋር በመተባበር ለድርጅቱ ደንበኞች የአጭር ጊዜ ብድር አገልግሎት አቅርቧል፡፡ አዋሽ ባንክ ይህንን የብድር አገልግሎት የሚሰጠው በኢትዮጵያ ምርት ገበያ ድርጅት እንዲገበያዩና በድርጅቱ መጋዘኖች እንዲከማቹ ለተፈቀደ የግብርና ግብዓቶች ሲሆን የብድር አገልግሎቱን ለማግኝት አምራቾቹ ባንኩ በብድር ፖሊሲው ያስቀመጣቸውን መስፈርቶች አሟልተው መገኘት አለባቸው፡፡
Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Jul 26, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
57.4895 58.6393
GBP
70.6759 72.0894
EUR
62.3359 63.5826
AED
14.1646 14.4479
SAR
13.8682 14.1456
CHF
62.5028 63.7529

Exchange Rate
Close