አዋሽ ባንክ የመጋዘን ደረሰኝ የብድር አገልግሎት መስጠት ጀመረ!

የመጋዘን ደረሰኝ ብድር አንድ አምራች ወይም ተገበያይ ምርቱን ወደ ኢትዮጵያ ምርት ገበያ መጋዘን በማስገባትና የመጋዘን ደረሰኙን (WR) እንደ ማስያዣ በመጠቀም ከምርት ገበያው ጋር በጣምራ ከሚሰሩ ባንኮች ብድር አገልግሎት የሚያገኝበት አሰራር ነው፡፡በዚህ መሰረት ተበዳሪው አርሶ አደር፣ የህብረት ስራ ማህበራት ዩኒየኖች እና አቅራቢዎች መያዣ እንዲሆን ካስገባው ምርት ውጭ ሌላ ንብረት ለመያዣነት ሳያስፈልገው ከባንክ የአጭር ጊዜ የብድር አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ፡፡
በዚሁ መሰረት አዋሽ ባንክ ከኢትዮጵያ የምርት ገበያ ድርጅት ጋር በመተባበር ለድርጅቱ ደንበኞች የአጭር ጊዜ ብድር አገልግሎት አቅርቧል፡፡ አዋሽ ባንክ ይህንን የብድር አገልግሎት የሚሰጠው በኢትዮጵያ ምርት ገበያ ድርጅት እንዲገበያዩና በድርጅቱ መጋዘኖች እንዲከማቹ ለተፈቀደ የግብርና ግብዓቶች ሲሆን የብድር አገልግሎቱን ለማግኝት አምራቾቹ ባንኩ በብድር ፖሊሲው ያስቀመጣቸውን መስፈርቶች አሟልተው መገኘት አለባቸው፡፡
Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

May 31, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
54.3041 55.3902
GBP
64.4469 65.7358
EUR
58.2683 59.4337
AED
13.3787 13.6463
SAR
13.1039 13.3660
CHF
57.4567 58.6058

Exchange Rate
Close