አዋሽ ባንክ ከሬይስ ማይክሮ ፋይናንስ ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡

አዋሽ ባንክ ከሬይስ ማይክሮ ፋይናንስ ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡

የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት የአዋሽ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እና  የሬይስ ማይክሮ ፋይናንስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አብዲአዚዝ ሀሰን ሲሆኑ ስምምነቱ በርካታ የፋይናንስ ስራዎችን በትብብር ለመስራት የሚያስችል መሆኑን የሁለቱ ተቋማት ኃላፊዎች ገልጸዋል፡፡የመግባቢያ ስምምነቱ ዋና ዓላማ ባንኩ ተደራሽነቱን በማስፋት እንዲሁም ከሬይስ ማይክሮ ፋይናንስ ጋር በመተባበር ማይክሮ ፋይናንሱ በሰፊው በሚንቀሳቀስባቸው በምስራቁ የሀገሪቱ ክፍል ለሚገኙና የባንክ አገልግሎት ተጠቃሚ ላልሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደየአካባቢው ነባራዊ ሁኔታ በቴክኖሎጂ የታገዘ አስተማማኝ የፋይናንስ አገልግሎት መስጠት እንደሆነም ተጠቁሟል።

አዋሽ ባንክ በምስራቅ የሀገራችን ክፍል ማለትም በድሬዳዋ፣ ጅግጅጋ እንዲሁም በቶጎጫሌ አካባቢ በቀዳሚነት ቅርንጫፎቹን የከፈተ የመጀመሪያው የግል ባንክ ነው፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Oct 25, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
119.2055 121.5896
GBP
146.5477 149.4786
EUR
129.2543 131.8394
AED
29.3709 29.9583
SAR
28.7559 29.3311
CHF
129.6006 132.1926

Exchange Rate
Close