አዋሽ ባንክ ከሬይስ ማይክሮ ፋይናንስ ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡

አዋሽ ባንክ ከሬይስ ማይክሮ ፋይናንስ ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡

የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት የአዋሽ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እና  የሬይስ ማይክሮ ፋይናንስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አብዲአዚዝ ሀሰን ሲሆኑ ስምምነቱ በርካታ የፋይናንስ ስራዎችን በትብብር ለመስራት የሚያስችል መሆኑን የሁለቱ ተቋማት ኃላፊዎች ገልጸዋል፡፡የመግባቢያ ስምምነቱ ዋና ዓላማ ባንኩ ተደራሽነቱን በማስፋት እንዲሁም ከሬይስ ማይክሮ ፋይናንስ ጋር በመተባበር ማይክሮ ፋይናንሱ በሰፊው በሚንቀሳቀስባቸው በምስራቁ የሀገሪቱ ክፍል ለሚገኙና የባንክ አገልግሎት ተጠቃሚ ላልሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደየአካባቢው ነባራዊ ሁኔታ በቴክኖሎጂ የታገዘ አስተማማኝ የፋይናንስ አገልግሎት መስጠት እንደሆነም ተጠቁሟል።

አዋሽ ባንክ በምስራቅ የሀገራችን ክፍል ማለትም በድሬዳዋ፣ ጅግጅጋ እንዲሁም በቶጎጫሌ አካባቢ በቀዳሚነት ቅርንጫፎቹን የከፈተ የመጀመሪያው የግል ባንክ ነው፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

May 31, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
54.3041 55.3902
GBP
64.4469 65.7358
EUR
58.2683 59.4337
AED
13.3787 13.6463
SAR
13.1039 13.3660
CHF
57.4567 58.6058

Exchange Rate
Close