አዋሽ ባንክ ከሬይስ ማይክሮ ፋይናንስ ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡

አዋሽ ባንክ ከሬይስ ማይክሮ ፋይናንስ ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡

የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት የአዋሽ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እና  የሬይስ ማይክሮ ፋይናንስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አብዲአዚዝ ሀሰን ሲሆኑ ስምምነቱ በርካታ የፋይናንስ ስራዎችን በትብብር ለመስራት የሚያስችል መሆኑን የሁለቱ ተቋማት ኃላፊዎች ገልጸዋል፡፡የመግባቢያ ስምምነቱ ዋና ዓላማ ባንኩ ተደራሽነቱን በማስፋት እንዲሁም ከሬይስ ማይክሮ ፋይናንስ ጋር በመተባበር ማይክሮ ፋይናንሱ በሰፊው በሚንቀሳቀስባቸው በምስራቁ የሀገሪቱ ክፍል ለሚገኙና የባንክ አገልግሎት ተጠቃሚ ላልሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደየአካባቢው ነባራዊ ሁኔታ በቴክኖሎጂ የታገዘ አስተማማኝ የፋይናንስ አገልግሎት መስጠት እንደሆነም ተጠቁሟል።

አዋሽ ባንክ በምስራቅ የሀገራችን ክፍል ማለትም በድሬዳዋ፣ ጅግጅጋ እንዲሁም በቶጎጫሌ አካባቢ በቀዳሚነት ቅርንጫፎቹን የከፈተ የመጀመሪያው የግል ባንክ ነው፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Jul 26, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
57.4895 58.6393
GBP
70.6759 72.0894
EUR
62.3359 63.5826
AED
14.1646 14.4479
SAR
13.8682 14.1456
CHF
62.5028 63.7529

Exchange Rate
Close