አዋሽ ባንክ ከሬይስ ማይክሮ ፋይናንስ ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡

አዋሽ ባንክ ከሬይስ ማይክሮ ፋይናንስ ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡

የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት የአዋሽ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እና  የሬይስ ማይክሮ ፋይናንስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አብዲአዚዝ ሀሰን ሲሆኑ ስምምነቱ በርካታ የፋይናንስ ስራዎችን በትብብር ለመስራት የሚያስችል መሆኑን የሁለቱ ተቋማት ኃላፊዎች ገልጸዋል፡፡የመግባቢያ ስምምነቱ ዋና ዓላማ ባንኩ ተደራሽነቱን በማስፋት እንዲሁም ከሬይስ ማይክሮ ፋይናንስ ጋር በመተባበር ማይክሮ ፋይናንሱ በሰፊው በሚንቀሳቀስባቸው በምስራቁ የሀገሪቱ ክፍል ለሚገኙና የባንክ አገልግሎት ተጠቃሚ ላልሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደየአካባቢው ነባራዊ ሁኔታ በቴክኖሎጂ የታገዘ አስተማማኝ የፋይናንስ አገልግሎት መስጠት እንደሆነም ተጠቁሟል።

አዋሽ ባንክ በምስራቅ የሀገራችን ክፍል ማለትም በድሬዳዋ፣ ጅግጅጋ እንዲሁም በቶጎጫሌ አካባቢ በቀዳሚነት ቅርንጫፎቹን የከፈተ የመጀመሪያው የግል ባንክ ነው፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Apr 18, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.8022 57.9382
GBP
67.5744 68.9259
EUR
60.4375 61.6463
AED
13.9956 14.2755
SAR
13.7039 13.9780
CHF
59.5391 60.7299

Exchange Rate
Close