አዋሽ ባንክ ከዘጠኝ አነስተኛ ፋይናንስ ተቋማት ጋር የብድር አቅርቦት ስምምነት አደረገ

አዋሽ ባንክ መካከለኛ፣ አነስተኛና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያገኙ ከዘጠኝ አነስተኛ ፋይናንስ ተቋማት ጋር የብድር አቅርቦት ስምምነት አድርጓል፡፡ ባንኩ ይህን ስምምነት ያደረገው ዘጠኙ አነስተኛ ፋይናንስ ተቋማትም፦ ቪዥን ፈንድ፣ ንስር፣ ቀንዲል፣ መተማመን፣ መክሊት፣ ዳይናሚክ፣ ዋሳሳ፣ ሃርቡ እና ፒስ አነስተኛ ፋይናንስ ተቋም ይገኙበታል።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የስራና ክህሎት ምኒስቴር ምኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈርሃት ካሚል እንደተናገሩት የመካከለኛ፣ አነስተኛና ጥቃቅን የሥራ ዘርፎች ለሥራ ዕድል ፈጠራ ፣ ለኢኮኖሚ ዕድገት እና ለማህበራዊ ችግሮች ማቃለያ ከፍተኛ ሚና ቢኖራቸውም ያላቸውን እምቅ አቅም ተጠቅመው ወደ ሥራ ለመግባት የፋይናንስ አቅርቦት ውስንነት እንዳለባቸው በመግለፅ ባንኩ ላደረገው የብድር ድጋፍ ምስጋናቸውን ያቀረቡ ሲሆን ሌሎች የፋይናንስ ተቋማትም ለዘርፉ እድገት አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Apr 25, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.8795 58.0171
GBP
67.5577 68.9089
EUR
60.7928 62.0087
AED
14.0132 14.2935
SAR
13.7240 13.9985
CHF
59.3920 60.5798

Exchange Rate
Close