አዋሽ ባንክ በከባድ ዝናብ ቤታቸው ለወደመባቸው አርሶ አደሮች የቆርቆሮ ድጋፍ አደረገ።

ለማህበረሰብ መቆርቆርን አንኳር እሴቱ ያደረገው አዋሽ ባንክ በምዕራብ ጎጃም ዞን ሰሜን ሜጫ ወረዳ በከባድ ዝናብ ቤታቸው ለወደመባቸው አርሶ አደሮች የቆርቆሮ ድጋፍ አድርጓል።
በሰሜን ሜጫ ወረዳ ሰኔ 4 እና ሰኔ 9/2014 ዓ.ም በጣለው በረዶ የቀላቀለ ዝናብ በ9 ቀበሌ 2ሺህ 631 አርሶ አደሮች የመኖሪያ ቤት፣ አትክልትና ፍራፍሬ ሌሎች ሰብሎችም ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን የተናገሩት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አንተነህ ወንዱ፣ አዋሽ ባንክ 1ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በሚሆን ወጪ ለተጎጂ አርሶ አደሮች ድጋፍ በማድረጉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
አዋሽ ባንክ ከምስረታው ጀምሮ የፋይናንስ አገልግሎቱን ተደራሽ ከማድረጉም ባሻገር በማንኛውም ወቅት ድንገተኛ አደጋዎች በሚያጋጥሙ ጊዜም ከማህበረሰቡ ጎን መቆሙን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዋሽ ባንክ ሰሜን ምዕራብ ሪጅን ዋና ዳይሬክተር አቶ መሠረት አምበሉ በድጋፍ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ገልፀዋል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

May 13, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.9632 58.1025
GBP
68.2066 69.5707
EUR
61.4063 62.6344
AED
14.0337 14.3144
SAR
13.7450 14.0199
CHF
60.0241 61.2246

Exchange Rate
Close