አዋሽ ባንክ በአምቦ ከተማ አዲስ ህንፃ ሊገነባ ነው

በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የክልል ከተሞች የራሱን ህንፃ በመገንባት የሚታወቀው አዋሽ ባንክ በአምቦ ከተማ ጠቅላላ የቦታው ስፋት 1,280 ካ.ሜትር ላይ የሚያርፍ እና ከምድር በታች ቤዝመንት ያለው ባለ ሰባት ወለል (G+7) አዲስ ዘመናዊ ህንፃ ለመገንባት የህንፃውን አርክቴክቸራል ዲዛይን ስራ አጠናቋል፡፡ ባንኩ የህንፃውን አርክቴክቸራል ዲዛይን ለማሰራት ባወጣው ጨረታ ተወዳድሮ ላሸነፈው አማካሪ ድርጅትም የእውቅና ሰርቲፍኬት እና የገንዘብ ሽልማት አበርክቷል::
ምንም እንኳን ከተወዳደሩት ድርጅቶች አንደኛ የወጣው በስራው ቢመረጥም በዘርፉ የተሰማሩ ድርጅቶችንም ለማበረታታት ሲባል አንደኛ ለወጣው የብር 125 ሺህ እንዲህም ሁለተኛ ለወጣው የብር 100 ሺህ የገንዘብ ሽልማትና የእውቅና ሰርቲፍኬት በባንኩ ተበርክቶላቸዋል፡፡ አዲሱ የአዋሽ ባንክ አምቦ ቅርንጫፍ ህንፃ ግንባታም በቅርቡ እንደሚጀመርና በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚውል የባንኩ ቺፍ ሆልሴል ባንኪንግ ኦፊሰር አቶ ታደሰ ገመዳ ተናግረዋል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Apr 30, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.9193 58.0577
GBP
68.1105 69.4727
EUR
61.0061 62.2262
AED
14.0233 14.3038
SAR
13.7339 14.0086
CHF
59.6356 60.8283

Exchange Rate
Close