አዋሽ ባንክ ከኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አቢያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ::

(ጥር 03 ቀን 2013 ዓ.ም አዋሽ ባንክ፣ አዲስ አበባ) አዋሽ ባንክ ከኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አቢያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።
የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት የአዋሽ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እና የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አቢያተ ክርስቲያናት ካውንስል ፕሬዝዳንት እያሱ ኤልያስ (ዶ/ር) ሲሆኑ በስምምነቱ ላይ ለእምነት ተቋማት ልዩ ትኩረት በመስጠት በርካታ የፋይናንስና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በሚያደርጉ እንዲሁም በተመረጡ የልማት ዘርፎች ዙሪያ በትብብር ለመስራት የሚያስችል መሆኑን የሁለቱ ተቋማት ኃላፊዎች ገልጸዋል፡፡
አዋሽ ባንክ የመንግስትን አቅጣጫ በመከተል ከበርካታ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነቶች በማድረግ ላይ ሲሆን በዚህም በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እየሆኑ ይገኛል።
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አቢያተ ክርስቲያናት ካውንስል በስሩ ከሰላሳ ሚሊዮን በላይ አባላትን ይዞ እንዲሁም ከሰላሳ አምስት ሺህ በላይ ቤተ-እምነቶችን በማቀፍ ከተመሰረተ ጥቂት ወራትን ያስቆጠረ ቢሆንም የጎልማሳ ራዕይን ሰንቆና ሀገራዊ ፋይዳውን በማሳደግ እንዲሁም አፍሪካንና ዓለም ዓቀፍ ገጽታን በመገንባት ከመንቀሳቀሱም ባሻገር ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሰፊ የልማት ሥራዎችና የአካባቢ ጥበቃ ላይ በመስራት ላይ የሚገኝ የእምነት ተቋማት ካውንስል ነው።
Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

May 02, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.9239 58.0624
GBP
68.1921 69.5559
EUR
61.0167 62.2370
AED
14.0245 14.3050
SAR
13.7344 14.0091
CHF
59.5882 60.7800

Exchange Rate
Close