አዋሽ ባንክ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የ 25 ሚሊዮን ብር የቦንድ ግዢ አከናወነ !

በአገራችን ኢኮኖሚ ውስጥ ጉልህ ሚና እየተጫወተ ያለውና ኮርፖሬት ማህበራዊ ኃላፊነቱን በተለያዩ ዘርፎች እየተወጣ ያለው ባንካችን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታው ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ቦንድ በመግዛትና ገንዘብ በመለገስ አስፈላጊውን የፋይናንስ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል፡፡ በዚህ የአገራችንን ታሪክ ከመሰረቱ እየቀየረ ባለው ታላቅ ፕሮጀክት ላይም ባንካችን የራሱን አሻራ እያኖረ በመሆኑም ደስታችን ወደር የለውም፡፡

ስለሆነም ልክ እንደ ከዚህ በፊቱ ሁሉ ዛሬም ታላቁ የአገራችን ህዳሴ እና ህልውና መሰረት የሆነው ግዳባችን አሁን ባለበት ደረጃ ላይ በመድረሱ ታላቅ ደስታ እንደተሰማን እየገለጽን ቀሪው ስራ በተያዘለት ዕቅድ መሰረት ተጠናቆ ለአገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የድርሻውን እንዲያበረክት፣ ህዝባችንም በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት አግኝቶ ኑሮውን እንዲያዘምን በባንካችን የዳይሬክተሮች ቦርድና የስራ አመራር ውሳኔ መሰረት የፋይናንስ ድጋፍ ለማድረግ በብር 25 ሚሊዮን የቦንድ ግዢ አከናውነናል፡፡ በዚህም የአገራችን የልማት አጋር በመሆናችን ታላቅ ኩራት ይሰማናል፡፡

 

 

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Apr 25, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.8795 58.0171
GBP
67.5577 68.9089
EUR
60.7928 62.0087
AED
14.0132 14.2935
SAR
13.7240 13.9985
CHF
59.3920 60.5798

Exchange Rate
Close