አዋሽ ባንክ በብድር ላይ የሚከፈለውን የወለድ ምጣኔ ዝቅ እንዲል አደረገ::

አዋሽ ባንክ በብድር ላይ የሚከፈለውን የወለድ ምጣኔ ዝቅ እንዲል አደረገ::

አዋሽ ባንክ በብድር ላይ የሚከፈለውን የወለድ ምጣኔ ከ 0.5%-4.5% ዝቅ እንዲል አድርጉዋል፡፡ ባንኩ በብድር ላይ የሚከፈለውን የወለድ ምጣኔ ከ 0.5% – 4.5% ዝቅ እንዲል ያደረጉት ዋና ዋና ምክንያቶች፡-

1. የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የቦንድ ግዥ መመሪያን ማሻሻሉ አዋሽ ባንክ ለቦንድ ግዥ  የሚያውለውን ገንዘብ ለብድር በማዋል ትርፋማነቱን በአስተማማኝ ሁኔታ መቀጠል የሚያስችለው መሆኑ በጥናት በመረጋገገጡ፣

2. በብድር ላይ የሚከፈለው የወለድ ምጣኔ ዝቅ መደረጉ በአገራችን እየታየ ያለውን የዋጋ  ግሽበት ለማስተካከል የራሱ የሆነ በጎ ተጽእኖ ይኖረዋል ተብሎ ስለታመነ፣

በአጠቃላይ የወለድ ምጣኔ ማስተካከያው የአገራችንን የኢንቨስትመንት እና የንግድ እንቅስቃሴ በማበረታታት ለአገራችን የኢኮኖሚ መረጋጋት የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ ይታመናል፡፡

የአዋሽ ባንክ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ቦንድ ግዥ እ.ኤ.አ ኦክቶበር፣ 2019 መጨረሻ ላይ ብር 12.4 ቢሊዮን ነበር፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Nov 28, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
55.6854 56.7991
GBP
67.1870 68.5307
EUR
60.9588 62.1780
AED
13.7216 13.9960
SAR
13.4363 13.7050
CHF
60.3764 61.5839

Exchange Rate
Close