አዋሽ ባንክ በብድር ላይ የሚከፈለውን የወለድ ምጣኔ ዝቅ እንዲል አደረገ::

አዋሽ ባንክ በብድር ላይ የሚከፈለውን የወለድ ምጣኔ ዝቅ እንዲል አደረገ::

አዋሽ ባንክ በብድር ላይ የሚከፈለውን የወለድ ምጣኔ ከ 0.5%-4.5% ዝቅ እንዲል አድርጉዋል፡፡ ባንኩ በብድር ላይ የሚከፈለውን የወለድ ምጣኔ ከ 0.5% – 4.5% ዝቅ እንዲል ያደረጉት ዋና ዋና ምክንያቶች፡-

1. የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የቦንድ ግዥ መመሪያን ማሻሻሉ አዋሽ ባንክ ለቦንድ ግዥ  የሚያውለውን ገንዘብ ለብድር በማዋል ትርፋማነቱን በአስተማማኝ ሁኔታ መቀጠል የሚያስችለው መሆኑ በጥናት በመረጋገገጡ፣

2. በብድር ላይ የሚከፈለው የወለድ ምጣኔ ዝቅ መደረጉ በአገራችን እየታየ ያለውን የዋጋ  ግሽበት ለማስተካከል የራሱ የሆነ በጎ ተጽእኖ ይኖረዋል ተብሎ ስለታመነ፣

በአጠቃላይ የወለድ ምጣኔ ማስተካከያው የአገራችንን የኢንቨስትመንት እና የንግድ እንቅስቃሴ በማበረታታት ለአገራችን የኢኮኖሚ መረጋጋት የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ ይታመናል፡፡

የአዋሽ ባንክ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ቦንድ ግዥ እ.ኤ.አ ኦክቶበር፣ 2019 መጨረሻ ላይ ብር 12.4 ቢሊዮን ነበር፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Jul 26, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
57.4895 58.6393
GBP
70.6759 72.0894
EUR
62.3359 63.5826
AED
14.1646 14.4479
SAR
13.8682 14.1456
CHF
62.5028 63.7529

Exchange Rate
Close