አዋሽ ባንክ በብድር ላይ የሚከፈለውን የወለድ ምጣኔ ዝቅ እንዲል አደረገ::

አዋሽ ባንክ በብድር ላይ የሚከፈለውን የወለድ ምጣኔ ዝቅ እንዲል አደረገ::

አዋሽ ባንክ በብድር ላይ የሚከፈለውን የወለድ ምጣኔ ከ 0.5%-4.5% ዝቅ እንዲል አድርጉዋል፡፡ ባንኩ በብድር ላይ የሚከፈለውን የወለድ ምጣኔ ከ 0.5% – 4.5% ዝቅ እንዲል ያደረጉት ዋና ዋና ምክንያቶች፡-

1. የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የቦንድ ግዥ መመሪያን ማሻሻሉ አዋሽ ባንክ ለቦንድ ግዥ  የሚያውለውን ገንዘብ ለብድር በማዋል ትርፋማነቱን በአስተማማኝ ሁኔታ መቀጠል የሚያስችለው መሆኑ በጥናት በመረጋገገጡ፣

2. በብድር ላይ የሚከፈለው የወለድ ምጣኔ ዝቅ መደረጉ በአገራችን እየታየ ያለውን የዋጋ  ግሽበት ለማስተካከል የራሱ የሆነ በጎ ተጽእኖ ይኖረዋል ተብሎ ስለታመነ፣

በአጠቃላይ የወለድ ምጣኔ ማስተካከያው የአገራችንን የኢንቨስትመንት እና የንግድ እንቅስቃሴ በማበረታታት ለአገራችን የኢኮኖሚ መረጋጋት የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ ይታመናል፡፡

የአዋሽ ባንክ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ቦንድ ግዥ እ.ኤ.አ ኦክቶበር፣ 2019 መጨረሻ ላይ ብር 12.4 ቢሊዮን ነበር፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Sep 07, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
115.1001 118.7426
GBP
141.5006 145.9786
EUR
124.8029 128.7525
AED
28.3594 29.2569
SAR
27.7656 28.6444
CHF
125.1372 129.0973

Exchange Rate
Close