አዋሽ ባንክ የኢፍጣር መርሐ-ግብር አካሄደ።

አዋሽ ባንክ የታላቁ የረመዳን ወርን በማስመልከት ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች መልካም ምኞቱን ለመግለጽና ለደንበኞቹ ያለውን አጋርነት ለማረጋገጥ በማሰብ በ ቀን 11,2014 ዓ.ም  በሸራተን አዲስ ሆቴል የጋራ የኢፍጣር ሥነ-ሥርዓት ያካሄደ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ባንኩ የሸሪአ መርሆችን መሰረት አድርጎ በማቅረብ ላይ በሚገኘው ‘’አዋሽ ኢኽላስ’’ የተሟላ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎቶች በተጨማሪ ኢጃራ ፋይናንሲንግ፣ ቃርዱል ሀሰን ፋይናንሲንግ እንዲሁም አል- ከይር ዋድያ (የተቀማጭ ሂሳብ) የተሰኙ አዳዲስ ፕሮዳክቶችን በይፋ አስጀምሯል፡፡

በመርሐ-ግብሩ ላይ የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሐይ ሽፈራውን ጨምሮ ፣ የአዋሽ ባንክ የሸሪዓ አማካሪዎች ፣ የባንኩ የሥራ አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን፣ ባንኩ በሸሪዓ መርሆች ላይ የተመሰረተውን የአዋሽ ኢኽላስ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ዓይነቶችና ተደራሽነት ለማስፋት ጠንክሮ እየሰራ መሆኑ ተገልጿል።

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Sep 21, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
55.1948 56.2987
GBP
65.1720 66.4754
EUR
59.0308 60.2114
AED
13.5981 13.8701
SAR
13.3154 13.5817
CHF
58.7571 59.9322

Exchange Rate
Close