አዋሽ ባንክ የመጋዘን ደረሰኝ የብድር አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል

የመጋዘን ደረሰኝ ብድር አንድ አምራች ወይም ተገበያይ ምርቱን ወደ ኢትዮጵያ ምርት ገበያ መጋዘን በማስገባትና የመጋዘን ደረሰኙን (WR) እንደ ማስያዣ በመጠቀም የሚያገኝ የብድር አገልግሎት ነው፡፡በዚህ መሰረት ተበዳሪው አርሶ አደር፣ የህብረት ስራ ማህበራት ዩኒየኖች እና አቅራቢዎች መያዣ እንዲሆን ካስገብት ምርት ውጭ ሌላ ንብረት ለመያዣነት ሳያስፈልጋቸው ከባንክ የአጭር ጊዜ የብድር አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ፡፡
በዚሁ መሰረት አዋሽ ባንክ ከኢትዮጵያ የምርት ገበያ ድርጅት ጋር በመተባበር ለድርጅቱ ደንበኞች የአጭር ጊዜ ብድር አገልግሎት ማቅረብ የጀመረ ሲሆን ይህንን የብድር አገልግሎት የሚሰጠው በኢትዮጵያ ምርት ገበያ ድርጅት እንዲገበያዩና በድርጅቱ መጋዘኖች እንዲከማቹ ለተፈቀደ የግብርና ምርቶች ነው፡፡ የብድር አገልግሎቱን ለማግኝት አምራቾቹ ባንኩ በብድር ፖሊሲው ያስቀመጣቸውን መስፈርቶች አሟልተው መገኘት አለባቸው፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Oct 18, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
119.0155 121.3958
GBP
146.3141 149.2403
EUR
129.0483 131.6293
AED
29.3241 29.9105
SAR
28.7101 29.2843
CHF
129.3940 131.9819

Exchange Rate
Close