አዋሽ ባንክ ከፍተኛ የወለድ ምጣኔ ቅነሳ አደረገ

በአለም ጤና ድርጅት በወረርሽኝነት የተፈረጀው የኮሮና ቫይረስ በዓለማችን ላይ ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ መተኪያ የሌለውን የሰው ልጅ ህይወት ከመቅጠፍም አልፎ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ድቀትን አስከትሏል፡፡ የተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች እንቅስቃሴዎችም ከመቀዛቀዛቸው የተነሳ በዓለማችን ላይ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችም ለስራ አጥነት ተዳርገዋል፡፡

ወረርሽኙ በአገራችን መከሰቱን የኢፌዲሪ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ካሳወቁበት ጊዜ አንስቶ በተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ እየተስተዋሉ ያሉ ተፅእኖዎች ቀላል የሚባሉ አይደሉም፡፡ ይህ ወረርሽኝ በንግድ እንቅስቃሴ ላይ የሚያሳድረውን ተፅእኖ ከግምት ውስጥ በማስገባት አዋሽ ባንክ በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ የተለያዩ ማሻሻያዎችን አድርጓል፡፡

በዚህም መሰረት የአዋሽ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድና ማነጅመንት ቫይረሱ በተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ እያደረሰ ያለውን ተፅእኖ ከገመገመ በኋላ በተለይም የችግሩ ቀጥተኛ ተፅእኖ ሰለባ ለሆኑት አገልግሎት ሰጪ ሴክተሮች ላይ ለተሳማሩት ተበዳሪ ደንበኞቹ ከፍተኛ የወለድ ምጣኔ ቅነሳ አድርጓል፡፡ የወለድ ምጣኔ ቅነሳው የተደረገላቸው የኢኮኖሚ ዘርፎችም የሆቴል እና ቱሪዝም፣ የጉዞና አስጎብኚ ድርጅቶች እና የአበባ አምራች ኢንዱስትሪዎች ሲሆኑ ለሆቴሎች ቀደም ሲል ከ12.5 እስከ 15.75 በመቶ ፣ ለጉዞና አስጎብኚ ድርጅቶችና ለአባባ አምራቾች ከ 9 እስከ 12.5 በመቶ የነበረው የወለድ ምጣኔ ለቀጣይ ሶስት ወራት ወደ ዝቅተኛው የወለድ ምጣኔ ማለትም ወደ (7%) ሰባት በመቶ እንዲቀንስላቸው ተደርጓል፡፡ ባንኩ ይህንን የወለድ ቅነሳ በማድረጉም በትንሹ እሰከ ብር 50 ሚሊዮን የሚደርስ ገቢ የሚያጣ ይሆናል፡፡

አዋሽ ባንክ የወረርሽኙን በአገራችን መከሰት ተከትሎ ቀደም ሲልም የኤልሲ ማራዘሚያ የኮሚሽን ክፍያ፣ በተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ለተሰማሩ ተበዳሪዎቹ የብድር መመለሻ ጊዜ ማራዘሚያ የኮሚሽን ክፍያ እና ኤቲኤም ለሚገለገሉ ደንበኞቹ ያስከፍል የነበረውን የአገልግሎት ክፍያ እ.አ.አ ከኤፕሪል 01/2020 ጀምሮ ለሁለት ተከታታይ ወራት ሙሉ በሙሉ ነፃ ማድረጉ ይታወሳል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Mar 09, 2026 - EXCHANGE Rate
CurrencyCash and Remittances through AgentsTransaction
BuyingSellingBuyingSelling
USD USD153.2439156.3088153.0141156.0744
GBP GBP207.4951211.6450207.4951211.6450
EUR EUR181.4794185.1090181.4794185.1090
JPY JPY1.01121.03141.01631.0366
SAR SAR43.084043.945743.587744.4595
AED AED44.022344.902744.539545.4303
CAD CAD111.3935113.6214112.6983114.9523
CHF CHF195.6127199.5250197.8906201.8484
NOK NOK14.737615.032413.697013.9709
DKK DKK23.213723.678023.485123.9548
SEK SEK17.027717.368317.226817.5713