አዋሽ ባንክ ከፍተኛ የወለድ ምጣኔ ቅነሳ አደረገ

በአለም ጤና ድርጅት በወረርሽኝነት የተፈረጀው የኮሮና ቫይረስ በዓለማችን ላይ ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ መተኪያ የሌለውን የሰው ልጅ ህይወት ከመቅጠፍም አልፎ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ድቀትን አስከትሏል፡፡ የተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች እንቅስቃሴዎችም ከመቀዛቀዛቸው የተነሳ በዓለማችን ላይ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችም ለስራ አጥነት ተዳርገዋል፡፡

ወረርሽኙ በአገራችን መከሰቱን የኢፌዲሪ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ካሳወቁበት ጊዜ አንስቶ በተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ እየተስተዋሉ ያሉ ተፅእኖዎች ቀላል የሚባሉ አይደሉም፡፡ ይህ ወረርሽኝ በንግድ እንቅስቃሴ ላይ የሚያሳድረውን ተፅእኖ ከግምት ውስጥ በማስገባት አዋሽ ባንክ በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ የተለያዩ ማሻሻያዎችን አድርጓል፡፡

በዚህም መሰረት የአዋሽ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድና ማነጅመንት ቫይረሱ በተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ እያደረሰ ያለውን ተፅእኖ ከገመገመ በኋላ በተለይም የችግሩ ቀጥተኛ ተፅእኖ ሰለባ ለሆኑት አገልግሎት ሰጪ ሴክተሮች ላይ ለተሳማሩት ተበዳሪ ደንበኞቹ ከፍተኛ የወለድ ምጣኔ ቅነሳ አድርጓል፡፡ የወለድ ምጣኔ ቅነሳው የተደረገላቸው የኢኮኖሚ ዘርፎችም የሆቴል እና ቱሪዝም፣ የጉዞና አስጎብኚ ድርጅቶች እና የአበባ አምራች ኢንዱስትሪዎች ሲሆኑ ለሆቴሎች ቀደም ሲል ከ12.5 እስከ 15.75 በመቶ ፣ ለጉዞና አስጎብኚ ድርጅቶችና ለአባባ አምራቾች ከ 9 እስከ 12.5 በመቶ የነበረው የወለድ ምጣኔ ለቀጣይ ሶስት ወራት ወደ ዝቅተኛው የወለድ ምጣኔ ማለትም ወደ (7%) ሰባት በመቶ እንዲቀንስላቸው ተደርጓል፡፡ ባንኩ ይህንን የወለድ ቅነሳ በማድረጉም በትንሹ እሰከ ብር 50 ሚሊዮን የሚደርስ ገቢ የሚያጣ ይሆናል፡፡

አዋሽ ባንክ የወረርሽኙን በአገራችን መከሰት ተከትሎ ቀደም ሲልም የኤልሲ ማራዘሚያ የኮሚሽን ክፍያ፣ በተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ለተሰማሩ ተበዳሪዎቹ የብድር መመለሻ ጊዜ ማራዘሚያ የኮሚሽን ክፍያ እና ኤቲኤም ለሚገለገሉ ደንበኞቹ ያስከፍል የነበረውን የአገልግሎት ክፍያ እ.አ.አ ከኤፕሪል 01/2020 ጀምሮ ለሁለት ተከታታይ ወራት ሙሉ በሙሉ ነፃ ማድረጉ ይታወሳል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

May 31, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
54.3041 55.3902
GBP
64.4469 65.7358
EUR
58.2683 59.4337
AED
13.3787 13.6463
SAR
13.1039 13.3660
CHF
57.4567 58.6058

Exchange Rate
Close