አዋሽ ባንክ ከዘጠኝ አነስተኛ ፋይናንስ ተቋማት ጋር የብድር አቅርቦት ስምምነት አደረገ

አዋሽ ባንክ መካከለኛ፣ አነስተኛና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያገኙ ከዘጠኝ አነስተኛ ፋይናንስ ተቋማት ጋር የብድር አቅርቦት ስምምነት አድርጓል፡፡ ባንኩ ይህን ስምምነት ያደረገው ዘጠኙ አነስተኛ ፋይናንስ ተቋማትም፦ ቪዥን ፈንድ፣ ንስር፣ ቀንዲል፣ መተማመን፣ መክሊት፣ ዳይናሚክ፣ ዋሳሳ፣ ሃርቡ እና ፒስ አነስተኛ ፋይናንስ ተቋም ይገኙበታል።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የስራና ክህሎት ምኒስቴር ምኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈርሃት ካሚል እንደተናገሩት የመካከለኛ፣ አነስተኛና ጥቃቅን የሥራ ዘርፎች ለሥራ ዕድል ፈጠራ ፣ ለኢኮኖሚ ዕድገት እና ለማህበራዊ ችግሮች ማቃለያ ከፍተኛ ሚና ቢኖራቸውም ያላቸውን እምቅ አቅም ተጠቅመው ወደ ሥራ ለመግባት የፋይናንስ አቅርቦት ውስንነት እንዳለባቸው በመግለፅ ባንኩ ላደረገው የብድር ድጋፍ ምስጋናቸውን ያቀረቡ ሲሆን ሌሎች የፋይናንስ ተቋማትም ለዘርፉ እድገት አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Jul 26, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
57.4895 58.6393
GBP
70.6759 72.0894
EUR
62.3359 63.5826
AED
14.1646 14.4479
SAR
13.8682 14.1456
CHF
62.5028 63.7529

Exchange Rate
Close