አዋሽ ባንክ ከዘጠኝ አነስተኛ ፋይናንስ ተቋማት ጋር የብድር አቅርቦት ስምምነት አደረገ

አዋሽ ባንክ መካከለኛ፣ አነስተኛና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያገኙ ከዘጠኝ አነስተኛ ፋይናንስ ተቋማት ጋር የብድር አቅርቦት ስምምነት አድርጓል፡፡ ባንኩ ይህን ስምምነት ያደረገው ዘጠኙ አነስተኛ ፋይናንስ ተቋማትም፦ ቪዥን ፈንድ፣ ንስር፣ ቀንዲል፣ መተማመን፣ መክሊት፣ ዳይናሚክ፣ ዋሳሳ፣ ሃርቡ እና ፒስ አነስተኛ ፋይናንስ ተቋም ይገኙበታል።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የስራና ክህሎት ምኒስቴር ምኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈርሃት ካሚል እንደተናገሩት የመካከለኛ፣ አነስተኛና ጥቃቅን የሥራ ዘርፎች ለሥራ ዕድል ፈጠራ ፣ ለኢኮኖሚ ዕድገት እና ለማህበራዊ ችግሮች ማቃለያ ከፍተኛ ሚና ቢኖራቸውም ያላቸውን እምቅ አቅም ተጠቅመው ወደ ሥራ ለመግባት የፋይናንስ አቅርቦት ውስንነት እንዳለባቸው በመግለፅ ባንኩ ላደረገው የብድር ድጋፍ ምስጋናቸውን ያቀረቡ ሲሆን ሌሎች የፋይናንስ ተቋማትም ለዘርፉ እድገት አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Sep 21, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
55.1948 56.2987
GBP
65.1720 66.4754
EUR
59.0308 60.2114
AED
13.5981 13.8701
SAR
13.3154 13.5817
CHF
58.7571 59.9322

Exchange Rate
Close