አዋሽ ባንክ ከኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አቢያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ::

(ጥር 03 ቀን 2013 ዓ.ም አዋሽ ባንክ፣ አዲስ አበባ) አዋሽ ባንክ ከኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አቢያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።
የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት የአዋሽ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እና የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አቢያተ ክርስቲያናት ካውንስል ፕሬዝዳንት እያሱ ኤልያስ (ዶ/ር) ሲሆኑ በስምምነቱ ላይ ለእምነት ተቋማት ልዩ ትኩረት በመስጠት በርካታ የፋይናንስና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በሚያደርጉ እንዲሁም በተመረጡ የልማት ዘርፎች ዙሪያ በትብብር ለመስራት የሚያስችል መሆኑን የሁለቱ ተቋማት ኃላፊዎች ገልጸዋል፡፡
አዋሽ ባንክ የመንግስትን አቅጣጫ በመከተል ከበርካታ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነቶች በማድረግ ላይ ሲሆን በዚህም በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እየሆኑ ይገኛል።
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አቢያተ ክርስቲያናት ካውንስል በስሩ ከሰላሳ ሚሊዮን በላይ አባላትን ይዞ እንዲሁም ከሰላሳ አምስት ሺህ በላይ ቤተ-እምነቶችን በማቀፍ ከተመሰረተ ጥቂት ወራትን ያስቆጠረ ቢሆንም የጎልማሳ ራዕይን ሰንቆና ሀገራዊ ፋይዳውን በማሳደግ እንዲሁም አፍሪካንና ዓለም ዓቀፍ ገጽታን በመገንባት ከመንቀሳቀሱም ባሻገር ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሰፊ የልማት ሥራዎችና የአካባቢ ጥበቃ ላይ በመስራት ላይ የሚገኝ የእምነት ተቋማት ካውንስል ነው።
Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Mar 09, 2026 - EXCHANGE Rate
CurrencyCash and Remittances through AgentsTransaction
BuyingSellingBuyingSelling
USD USD153.2439156.3088153.0141156.0744
GBP GBP207.4951211.6450207.4951211.6450
EUR EUR181.4794185.1090181.4794185.1090
JPY JPY1.01121.03141.01631.0366
SAR SAR43.084043.945743.587744.4595
AED AED44.022344.902744.539545.4303
CAD CAD111.3935113.6214112.6983114.9523
CHF CHF195.6127199.5250197.8906201.8484
NOK NOK14.737615.032413.697013.9709
DKK DKK23.213723.678023.485123.9548
SEK SEK17.027717.368317.226817.5713