አዋሽ ባንክ ከኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አቢያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ::

(ጥር 03 ቀን 2013 ዓ.ም አዋሽ ባንክ፣ አዲስ አበባ) አዋሽ ባንክ ከኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አቢያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።
የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት የአዋሽ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እና የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አቢያተ ክርስቲያናት ካውንስል ፕሬዝዳንት እያሱ ኤልያስ (ዶ/ር) ሲሆኑ በስምምነቱ ላይ ለእምነት ተቋማት ልዩ ትኩረት በመስጠት በርካታ የፋይናንስና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በሚያደርጉ እንዲሁም በተመረጡ የልማት ዘርፎች ዙሪያ በትብብር ለመስራት የሚያስችል መሆኑን የሁለቱ ተቋማት ኃላፊዎች ገልጸዋል፡፡
አዋሽ ባንክ የመንግስትን አቅጣጫ በመከተል ከበርካታ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነቶች በማድረግ ላይ ሲሆን በዚህም በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እየሆኑ ይገኛል።
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አቢያተ ክርስቲያናት ካውንስል በስሩ ከሰላሳ ሚሊዮን በላይ አባላትን ይዞ እንዲሁም ከሰላሳ አምስት ሺህ በላይ ቤተ-እምነቶችን በማቀፍ ከተመሰረተ ጥቂት ወራትን ያስቆጠረ ቢሆንም የጎልማሳ ራዕይን ሰንቆና ሀገራዊ ፋይዳውን በማሳደግ እንዲሁም አፍሪካንና ዓለም ዓቀፍ ገጽታን በመገንባት ከመንቀሳቀሱም ባሻገር ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሰፊ የልማት ሥራዎችና የአካባቢ ጥበቃ ላይ በመስራት ላይ የሚገኝ የእምነት ተቋማት ካውንስል ነው።
Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

May 31, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
54.3041 55.3902
GBP
64.4469 65.7358
EUR
58.2683 59.4337
AED
13.3787 13.6463
SAR
13.1039 13.3660
CHF
57.4567 58.6058

Exchange Rate
Close