አዋሽ ባንክ ከኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አቢያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ::

(ጥር 03 ቀን 2013 ዓ.ም አዋሽ ባንክ፣ አዲስ አበባ) አዋሽ ባንክ ከኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አቢያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።
የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት የአዋሽ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እና የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አቢያተ ክርስቲያናት ካውንስል ፕሬዝዳንት እያሱ ኤልያስ (ዶ/ር) ሲሆኑ በስምምነቱ ላይ ለእምነት ተቋማት ልዩ ትኩረት በመስጠት በርካታ የፋይናንስና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በሚያደርጉ እንዲሁም በተመረጡ የልማት ዘርፎች ዙሪያ በትብብር ለመስራት የሚያስችል መሆኑን የሁለቱ ተቋማት ኃላፊዎች ገልጸዋል፡፡
አዋሽ ባንክ የመንግስትን አቅጣጫ በመከተል ከበርካታ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነቶች በማድረግ ላይ ሲሆን በዚህም በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እየሆኑ ይገኛል።
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አቢያተ ክርስቲያናት ካውንስል በስሩ ከሰላሳ ሚሊዮን በላይ አባላትን ይዞ እንዲሁም ከሰላሳ አምስት ሺህ በላይ ቤተ-እምነቶችን በማቀፍ ከተመሰረተ ጥቂት ወራትን ያስቆጠረ ቢሆንም የጎልማሳ ራዕይን ሰንቆና ሀገራዊ ፋይዳውን በማሳደግ እንዲሁም አፍሪካንና ዓለም ዓቀፍ ገጽታን በመገንባት ከመንቀሳቀሱም ባሻገር ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሰፊ የልማት ሥራዎችና የአካባቢ ጥበቃ ላይ በመስራት ላይ የሚገኝ የእምነት ተቋማት ካውንስል ነው።
Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Sep 29, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
55.2224 56.3268
GBP
64.2394 65.5242
EUR
58.5247 59.6952
AED
13.6041 13.8762
SAR
13.3217 13.5881
CHF
57.7817 58.9373

Exchange Rate
Close