አዋሽ ባንክ እና የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።

አዋሽ ባንክ በሃገራችን እየተስፋፋ የመጣውንና በተለይ ባንኮችን ተጋላጭ የሚያደርገውን በውክልና ሰነዶች የማጭበርበር ወንጀል ለመከላከል የሚያስችለውን የመግባቢያ ሰነድ ከፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ ጋር ነሃሴ 24 ቀን 2013 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል ተፈራርሟል። የመግባቢያ ሰነዱን የፈረሙት የአዋሽ ባንክ ሆል ሴል ባንኪንግ ቺፍ ኦፊሰር አቶ ታደሰ ገመዳ እና የፌዴራል የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን አማረ ናቸው፡፡
ስምምነቱ በተለይም የዉክልና ሰነዶችን ትክክለኛነትና ህጋዊነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል በመሆኑ ከፍተኛ የማጭበርበር ወንጀሎችን ለማስቀረት የሚያስችል መሆኑን የመግባቢያ ስምምነቱን የተፈራረሙት የኤጀንሲዉ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን አማረና የአዋሽ ባንክ ሆል ሴል ባንኪንግ ቺፍ ኦፊሰር አቶ ታደሰ ገመዳ ገልፀዋል። ስምምነቱ ቀደም ሲል በዉክልና የሚንቀሳቀሱ የባንክ ሂሳቦችንና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ የዉክልናዉን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ በባንክ ባለሙያዎች ወደ ኤጀንሲዉ ይደወል የነበረዉን በማስቀረት ኦንላይን ለማረጋገጥ ስለሚያስችል ቀደም ሲል የነበረዉን እንግልትና የተንዛዛ አሰራር ሙሉ በመሉ የሚያስቀር ነዉ ተብሏል።

 

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Sep 29, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
55.2224 56.3268
GBP
64.2394 65.5242
EUR
58.5247 59.6952
AED
13.6041 13.8762
SAR
13.3217 13.5881
CHF
57.7817 58.9373

Exchange Rate
Close