አዋሽ ባንክ እና የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።

አዋሽ ባንክ በሃገራችን እየተስፋፋ የመጣውንና በተለይ ባንኮችን ተጋላጭ የሚያደርገውን በውክልና ሰነዶች የማጭበርበር ወንጀል ለመከላከል የሚያስችለውን የመግባቢያ ሰነድ ከፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ ጋር ነሃሴ 24 ቀን 2013 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል ተፈራርሟል። የመግባቢያ ሰነዱን የፈረሙት የአዋሽ ባንክ ሆል ሴል ባንኪንግ ቺፍ ኦፊሰር አቶ ታደሰ ገመዳ እና የፌዴራል የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን አማረ ናቸው፡፡
ስምምነቱ በተለይም የዉክልና ሰነዶችን ትክክለኛነትና ህጋዊነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል በመሆኑ ከፍተኛ የማጭበርበር ወንጀሎችን ለማስቀረት የሚያስችል መሆኑን የመግባቢያ ስምምነቱን የተፈራረሙት የኤጀንሲዉ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን አማረና የአዋሽ ባንክ ሆል ሴል ባንኪንግ ቺፍ ኦፊሰር አቶ ታደሰ ገመዳ ገልፀዋል። ስምምነቱ ቀደም ሲል በዉክልና የሚንቀሳቀሱ የባንክ ሂሳቦችንና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ የዉክልናዉን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ በባንክ ባለሙያዎች ወደ ኤጀንሲዉ ይደወል የነበረዉን በማስቀረት ኦንላይን ለማረጋገጥ ስለሚያስችል ቀደም ሲል የነበረዉን እንግልትና የተንዛዛ አሰራር ሙሉ በመሉ የሚያስቀር ነዉ ተብሏል።

Mar 09, 2026 - EXCHANGE Rate
CurrencyCash and Remittances through AgentsTransaction
BuyingSellingBuyingSelling
USD USD153.2439156.3088153.0141156.0744
GBP GBP207.4951211.6450207.4951211.6450
EUR EUR181.4794185.1090181.4794185.1090
JPY JPY1.01121.03141.01631.0366
SAR SAR43.084043.945743.587744.4595
AED AED44.022344.902744.539545.4303
CAD CAD111.3935113.6214112.6983114.9523
CHF CHF195.6127199.5250197.8906201.8484
NOK NOK14.737615.032413.697013.9709
DKK DKK23.213723.678023.485123.9548
SEK SEK17.027717.368317.226817.5713