አዋሽ ባንክ እና የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።

አዋሽ ባንክ በሃገራችን እየተስፋፋ የመጣውንና በተለይ ባንኮችን ተጋላጭ የሚያደርገውን በውክልና ሰነዶች የማጭበርበር ወንጀል ለመከላከል የሚያስችለውን የመግባቢያ ሰነድ ከፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ ጋር ነሃሴ 24 ቀን 2013 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል ተፈራርሟል። የመግባቢያ ሰነዱን የፈረሙት የአዋሽ ባንክ ሆል ሴል ባንኪንግ ቺፍ ኦፊሰር አቶ ታደሰ ገመዳ እና የፌዴራል የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን አማረ ናቸው፡፡
ስምምነቱ በተለይም የዉክልና ሰነዶችን ትክክለኛነትና ህጋዊነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል በመሆኑ ከፍተኛ የማጭበርበር ወንጀሎችን ለማስቀረት የሚያስችል መሆኑን የመግባቢያ ስምምነቱን የተፈራረሙት የኤጀንሲዉ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን አማረና የአዋሽ ባንክ ሆል ሴል ባንኪንግ ቺፍ ኦፊሰር አቶ ታደሰ ገመዳ ገልፀዋል። ስምምነቱ ቀደም ሲል በዉክልና የሚንቀሳቀሱ የባንክ ሂሳቦችንና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ የዉክልናዉን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ በባንክ ባለሙያዎች ወደ ኤጀንሲዉ ይደወል የነበረዉን በማስቀረት ኦንላይን ለማረጋገጥ ስለሚያስችል ቀደም ሲል የነበረዉን እንግልትና የተንዛዛ አሰራር ሙሉ በመሉ የሚያስቀር ነዉ ተብሏል።

 

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Oct 25, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
119.2055 121.5896
GBP
146.5477 149.4786
EUR
129.2543 131.8394
AED
29.3709 29.9583
SAR
28.7559 29.3311
CHF
129.6006 132.1926

Exchange Rate
Close