አዋሽ ባንክ በኮርፖሬት ማህበራዊ ኃላፊነት መርሐ ግብሩ በበጎ አድራጎትና የማህበረሰብ ልማት ስራዎች ላይ ለተሰማሩ ስድስት የተለያዩ ድርጅቶች ብር 17.9 ሚሊዮን የገንዘብ ድጋፍ አደረገ፡፡

ባንካችን ላለፉት ዓመታት በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ በመመደብ በበርካታ የልማት፣ የሰብዓዊ ዕርዳታና የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች ላይ ተሳትፎ አድርጓል፤ አሁንም በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
የአዋሽ ባንክ ባለአክሲዮኖች እና ባንኩን በበላይነት የሚመራው የዳይሬክተሮች ቦርድ የባንኩ የማህበራዊ ኃላፊነት ግዴታ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ካላቸው ከፍተኛ ፍላጎት የተነሳ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በየዓመቱ ከፍተኛ በጀት በመመደብ የሚጠበቅበትን ማህበራዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ በማድረግ ባንኩ በህብረተሰቡ ዘንድም ሆነ በየደረጃው ካሉት የመንግስት ተቋማት ዘንድ መልካም ዝናን እንዲያተርፍ አድርገዋል፡፡
Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Jan 22, 2025 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
124.7041 127.1982
GBP
153.3074 156.3736
EUR
135.2163 137.9206
AED
30.7258 31.3403
SAR
30.0824 30.6841
CHF
135.5787 138.2902