አዋሽ ባንክ በከባድ ዝናብ ቤታቸው ለወደመባቸው አርሶ አደሮች የቆርቆሮ ድጋፍ አደረገ።

ለማህበረሰብ መቆርቆርን አንኳር እሴቱ ያደረገው አዋሽ ባንክ በምዕራብ ጎጃም ዞን ሰሜን ሜጫ ወረዳ በከባድ ዝናብ ቤታቸው ለወደመባቸው አርሶ አደሮች የቆርቆሮ ድጋፍ አድርጓል።
በሰሜን ሜጫ ወረዳ ሰኔ 4 እና ሰኔ 9/2014 ዓ.ም በጣለው በረዶ የቀላቀለ ዝናብ በ9 ቀበሌ 2ሺህ 631 አርሶ አደሮች የመኖሪያ ቤት፣ አትክልትና ፍራፍሬ ሌሎች ሰብሎችም ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን የተናገሩት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አንተነህ ወንዱ፣ አዋሽ ባንክ 1ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በሚሆን ወጪ ለተጎጂ አርሶ አደሮች ድጋፍ በማድረጉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
አዋሽ ባንክ ከምስረታው ጀምሮ የፋይናንስ አገልግሎቱን ተደራሽ ከማድረጉም ባሻገር በማንኛውም ወቅት ድንገተኛ አደጋዎች በሚያጋጥሙ ጊዜም ከማህበረሰቡ ጎን መቆሙን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዋሽ ባንክ ሰሜን ምዕራብ ሪጅን ዋና ዳይሬክተር አቶ መሠረት አምበሉ በድጋፍ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ገልፀዋል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Oct 25, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
119.2055 121.5896
GBP
146.5477 149.4786
EUR
129.2543 131.8394
AED
29.3709 29.9583
SAR
28.7559 29.3311
CHF
129.6006 132.1926

Exchange Rate
Close