አዋሽ ባንክ በከባድ ዝናብ ቤታቸው ለወደመባቸው አርሶ አደሮች የቆርቆሮ ድጋፍ አደረገ።

ለማህበረሰብ መቆርቆርን አንኳር እሴቱ ያደረገው አዋሽ ባንክ በምዕራብ ጎጃም ዞን ሰሜን ሜጫ ወረዳ በከባድ ዝናብ ቤታቸው ለወደመባቸው አርሶ አደሮች የቆርቆሮ ድጋፍ አድርጓል።
በሰሜን ሜጫ ወረዳ ሰኔ 4 እና ሰኔ 9/2014 ዓ.ም በጣለው በረዶ የቀላቀለ ዝናብ በ9 ቀበሌ 2ሺህ 631 አርሶ አደሮች የመኖሪያ ቤት፣ አትክልትና ፍራፍሬ ሌሎች ሰብሎችም ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን የተናገሩት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አንተነህ ወንዱ፣ አዋሽ ባንክ 1ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በሚሆን ወጪ ለተጎጂ አርሶ አደሮች ድጋፍ በማድረጉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
አዋሽ ባንክ ከምስረታው ጀምሮ የፋይናንስ አገልግሎቱን ተደራሽ ከማድረጉም ባሻገር በማንኛውም ወቅት ድንገተኛ አደጋዎች በሚያጋጥሙ ጊዜም ከማህበረሰቡ ጎን መቆሙን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዋሽ ባንክ ሰሜን ምዕራብ ሪጅን ዋና ዳይሬክተር አቶ መሠረት አምበሉ በድጋፍ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ገልፀዋል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Jul 26, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
57.4895 58.6393
GBP
70.6759 72.0894
EUR
62.3359 63.5826
AED
14.1646 14.4479
SAR
13.8682 14.1456
CHF
62.5028 63.7529

Exchange Rate
Close