አዋሽ ባንክ “በአዋሽ ይቆጥቡ ይቀበሉ ይሸለሙ” አሸናፊ ለሆኑ እድለኞች ያዘጋጀዉን ሽልማት አስረከበ

አዋሽ ባንክ ከግንቦት 17 ቀን 2013 ዓ.ም አስከ ጥር 11 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ ሲያካሂድ የነበረውን የ9ኛው ዙር “በአዋሽ ይቆጥቡ ይቀበሉ ይሸለሙ” የሎተሪ መርሐ ግብር አሸናፊ ለሆኑ እድለኞች ያዘጋጀዉን ሽልማት አስረከበ፡፡
ለዘጠነኛው ዙር መርሐ ግብር የተዘጋጁት የሽልማት ዓይነቶች በአምስት ደረጃዎች የተከፋፈሉ ሲሆን ለአንደኛው ዕጣ የተዘጋጀው የሽልማት ዓይነት አንድ አይሱዙ ዘመናዊ የጭነት መኪና የሎተሪ ቁጥር 00027805864 የያዙት አቶ ሀብታሙ ወልዴ ፋንታሁን በጅማ ከተማ ጅሬን ቅርንጫፍ የባንክ አገልግሎት ባገኙበት ወቅት በተሰጣቸው የሎተሪ ዕጣ ቁጥር አሸናፊ ሆነዋል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ለ2ኛ እጣ የተዘጋጀው ኪያ ፒካንቶ የቤት አውቶሞቢል የሎተሪ ቁጥር 00027414628 የያዙት አቶ በላቸው ስሜ አዱኛ ከገርባ ጉራቻ ከተማ ከገርባ ጉራቻ ቅርንጫፍ የደረሳቸው ሲሆን ለሶስተኛ ዕጣ (አስር ዕጣዎች) እያንዳንዳቸው ዘመናዊ ላፕቶፖች፣ ለአራተኛ ዕጣ (ሰላሳ ዕጣዎች) እያንዳንዳቸው 32 ኢንች ኤልኢዲ ቴሌቪዥኖች እንዲሁም ለአምስተኛ እጣ (ሀምሳ ዕጣዎች) እያንዳንዳቸው ስማርት የሞባይል ስልክ ቀፎዎችን ዕጣ ለወጣላቸው ለዕድለኞች ሽልማታቸውን አስረክቧል፡፡
በሽልማት አሰጣጥ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፀሐይ ሽፈራው ለሎተሪ ዕጣ አሸናፊዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ እንደገለፁት ባንኩ ያዘጋጀው የሎተሪ መርሐ ግብር የማህበረሰቡን የቁጠባ ባህል በማሳደግ የተሻለ የኑሮ ደረጃ ላይ እንዲደርሱ ግንዛቤን ከመፍጠሩም ባሻገር ለአገራችን የኢኮኖሚ ዕድገት አስፈላጊ እና ወሳኝ የሆነውን የውጭ ምንዛሪ ፍሰት በሕጋዊ መንገድ እንዲመጣ በማድረግ የሚገኘውም የውጭ ምንዛሪ ለአገራችን ልማትና ዕድገት እንዲውል ለማስቻል የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ረገድ ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው ለመርሐ ግብሩ መሳካት ያልተቆጠበ ድጋፍ ላደረጉት የመንግስት፣ የግል ድርጅቶችና ግለሰቦችን ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Oct 18, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
119.0155 121.3958
GBP
146.3141 149.2403
EUR
129.0483 131.6293
AED
29.3241 29.9105
SAR
28.7101 29.2843
CHF
129.3940 131.9819

Exchange Rate
Close