አዋሽ ባንክ በአምቦ ከተማ አዲስ ህንፃ ሊገነባ ነው

በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የክልል ከተሞች የራሱን ህንፃ በመገንባት የሚታወቀው አዋሽ ባንክ በአምቦ ከተማ ጠቅላላ የቦታው ስፋት 1,280 ካ.ሜትር ላይ የሚያርፍ እና ከምድር በታች ቤዝመንት ያለው ባለ ሰባት ወለል (G+7) አዲስ ዘመናዊ ህንፃ ለመገንባት የህንፃውን አርክቴክቸራል ዲዛይን ስራ አጠናቋል፡፡ ባንኩ የህንፃውን አርክቴክቸራል ዲዛይን ለማሰራት ባወጣው ጨረታ ተወዳድሮ ላሸነፈው አማካሪ ድርጅትም የእውቅና ሰርቲፍኬት እና የገንዘብ ሽልማት አበርክቷል::
ምንም እንኳን ከተወዳደሩት ድርጅቶች አንደኛ የወጣው በስራው ቢመረጥም በዘርፉ የተሰማሩ ድርጅቶችንም ለማበረታታት ሲባል አንደኛ ለወጣው የብር 125 ሺህ እንዲህም ሁለተኛ ለወጣው የብር 100 ሺህ የገንዘብ ሽልማትና የእውቅና ሰርቲፍኬት በባንኩ ተበርክቶላቸዋል፡፡ አዲሱ የአዋሽ ባንክ አምቦ ቅርንጫፍ ህንፃ ግንባታም በቅርቡ እንደሚጀመርና በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚውል የባንኩ ቺፍ ሆልሴል ባንኪንግ ኦፊሰር አቶ ታደሰ ገመዳ ተናግረዋል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

May 31, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
54.3041 55.3902
GBP
64.4469 65.7358
EUR
58.2683 59.4337
AED
13.3787 13.6463
SAR
13.1039 13.3660
CHF
57.4567 58.6058

Exchange Rate
Close