አዋሽ ባንክ በአምቦ ከተማ አዲስ ህንፃ ሊገነባ ነው

በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የክልል ከተሞች የራሱን ህንፃ በመገንባት የሚታወቀው አዋሽ ባንክ በአምቦ ከተማ ጠቅላላ የቦታው ስፋት 1,280 ካ.ሜትር ላይ የሚያርፍ እና ከምድር በታች ቤዝመንት ያለው ባለ ሰባት ወለል (G+7) አዲስ ዘመናዊ ህንፃ ለመገንባት የህንፃውን አርክቴክቸራል ዲዛይን ስራ አጠናቋል፡፡ ባንኩ የህንፃውን አርክቴክቸራል ዲዛይን ለማሰራት ባወጣው ጨረታ ተወዳድሮ ላሸነፈው አማካሪ ድርጅትም የእውቅና ሰርቲፍኬት እና የገንዘብ ሽልማት አበርክቷል::
ምንም እንኳን ከተወዳደሩት ድርጅቶች አንደኛ የወጣው በስራው ቢመረጥም በዘርፉ የተሰማሩ ድርጅቶችንም ለማበረታታት ሲባል አንደኛ ለወጣው የብር 125 ሺህ እንዲህም ሁለተኛ ለወጣው የብር 100 ሺህ የገንዘብ ሽልማትና የእውቅና ሰርቲፍኬት በባንኩ ተበርክቶላቸዋል፡፡ አዲሱ የአዋሽ ባንክ አምቦ ቅርንጫፍ ህንፃ ግንባታም በቅርቡ እንደሚጀመርና በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚውል የባንኩ ቺፍ ሆልሴል ባንኪንግ ኦፊሰር አቶ ታደሰ ገመዳ ተናግረዋል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Sep 07, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
115.1001 118.7426
GBP
141.5006 145.9786
EUR
124.8029 128.7525
AED
28.3594 29.2569
SAR
27.7656 28.6444
CHF
125.1372 129.0973

Exchange Rate
Close