አዋሽ ባንክ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የ 25 ሚሊዮን ብር የቦንድ ግዢ አከናወነ !

በአገራችን ኢኮኖሚ ውስጥ ጉልህ ሚና እየተጫወተ ያለውና ኮርፖሬት ማህበራዊ ኃላፊነቱን በተለያዩ ዘርፎች እየተወጣ ያለው ባንካችን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታው ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ቦንድ በመግዛትና ገንዘብ በመለገስ አስፈላጊውን የፋይናንስ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል፡፡ በዚህ የአገራችንን ታሪክ ከመሰረቱ እየቀየረ ባለው ታላቅ ፕሮጀክት ላይም ባንካችን የራሱን አሻራ እያኖረ በመሆኑም ደስታችን ወደር የለውም፡፡

ስለሆነም ልክ እንደ ከዚህ በፊቱ ሁሉ ዛሬም ታላቁ የአገራችን ህዳሴ እና ህልውና መሰረት የሆነው ግዳባችን አሁን ባለበት ደረጃ ላይ በመድረሱ ታላቅ ደስታ እንደተሰማን እየገለጽን ቀሪው ስራ በተያዘለት ዕቅድ መሰረት ተጠናቆ ለአገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የድርሻውን እንዲያበረክት፣ ህዝባችንም በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት አግኝቶ ኑሮውን እንዲያዘምን በባንካችን የዳይሬክተሮች ቦርድና የስራ አመራር ውሳኔ መሰረት የፋይናንስ ድጋፍ ለማድረግ በብር 25 ሚሊዮን የቦንድ ግዢ አከናውነናል፡፡ በዚህም የአገራችን የልማት አጋር በመሆናችን ታላቅ ኩራት ይሰማናል፡፡

 

 

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Feb 12, 2025 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
124.9998 127.4998
GBP
153.3074 156.3735
EUR
135.5371 138.2478
JPY
0.7393 0.7541
SAR
30.0824 30.6841
AED
30.7258 31.3403
CAD
81.5563 83.1874
CHF
135.5787 138.2902
NOK
10.1355 10.3382
DKK
16.4011 16.7291