አዋሽ ባንክ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የ 25 ሚሊዮን ብር የቦንድ ግዢ አከናወነ !

በአገራችን ኢኮኖሚ ውስጥ ጉልህ ሚና እየተጫወተ ያለውና ኮርፖሬት ማህበራዊ ኃላፊነቱን በተለያዩ ዘርፎች እየተወጣ ያለው ባንካችን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታው ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ቦንድ በመግዛትና ገንዘብ በመለገስ አስፈላጊውን የፋይናንስ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል፡፡ በዚህ የአገራችንን ታሪክ ከመሰረቱ እየቀየረ ባለው ታላቅ ፕሮጀክት ላይም ባንካችን የራሱን አሻራ እያኖረ በመሆኑም ደስታችን ወደር የለውም፡፡

ስለሆነም ልክ እንደ ከዚህ በፊቱ ሁሉ ዛሬም ታላቁ የአገራችን ህዳሴ እና ህልውና መሰረት የሆነው ግዳባችን አሁን ባለበት ደረጃ ላይ በመድረሱ ታላቅ ደስታ እንደተሰማን እየገለጽን ቀሪው ስራ በተያዘለት ዕቅድ መሰረት ተጠናቆ ለአገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የድርሻውን እንዲያበረክት፣ ህዝባችንም በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት አግኝቶ ኑሮውን እንዲያዘምን በባንካችን የዳይሬክተሮች ቦርድና የስራ አመራር ውሳኔ መሰረት የፋይናንስ ድጋፍ ለማድረግ በብር 25 ሚሊዮን የቦንድ ግዢ አከናውነናል፡፡ በዚህም የአገራችን የልማት አጋር በመሆናችን ታላቅ ኩራት ይሰማናል፡፡

 

 

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Nov 28, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
55.6854 56.7991
GBP
67.1870 68.5307
EUR
60.9588 62.1780
AED
13.7216 13.9960
SAR
13.4363 13.7050
CHF
60.3764 61.5839

Exchange Rate
Close