አዋሽ ባንክ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የ 25 ሚሊዮን ብር የቦንድ ግዢ አከናወነ !

በአገራችን ኢኮኖሚ ውስጥ ጉልህ ሚና እየተጫወተ ያለውና ኮርፖሬት ማህበራዊ ኃላፊነቱን በተለያዩ ዘርፎች እየተወጣ ያለው ባንካችን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታው ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ቦንድ በመግዛትና ገንዘብ በመለገስ አስፈላጊውን የፋይናንስ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል፡፡ በዚህ የአገራችንን ታሪክ ከመሰረቱ እየቀየረ ባለው ታላቅ ፕሮጀክት ላይም ባንካችን የራሱን አሻራ እያኖረ በመሆኑም ደስታችን ወደር የለውም፡፡

ስለሆነም ልክ እንደ ከዚህ በፊቱ ሁሉ ዛሬም ታላቁ የአገራችን ህዳሴ እና ህልውና መሰረት የሆነው ግዳባችን አሁን ባለበት ደረጃ ላይ በመድረሱ ታላቅ ደስታ እንደተሰማን እየገለጽን ቀሪው ስራ በተያዘለት ዕቅድ መሰረት ተጠናቆ ለአገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የድርሻውን እንዲያበረክት፣ ህዝባችንም በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት አግኝቶ ኑሮውን እንዲያዘምን በባንካችን የዳይሬክተሮች ቦርድና የስራ አመራር ውሳኔ መሰረት የፋይናንስ ድጋፍ ለማድረግ በብር 25 ሚሊዮን የቦንድ ግዢ አከናውነናል፡፡ በዚህም የአገራችን የልማት አጋር በመሆናችን ታላቅ ኩራት ይሰማናል፡፡

 

 

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Jul 26, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
57.4895 58.6393
GBP
70.6759 72.0894
EUR
62.3359 63.5826
AED
14.1646 14.4479
SAR
13.8682 14.1456
CHF
62.5028 63.7529

Exchange Rate
Close