አዋሽ ባንክ በባሌ ሮቤ ከተማ ያስገነባውን ህንፃ አስመረቀ

በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የክልል ከተሞች የራሱን ህንፃ በመገንባት የሚታወቀው አዋሽ ባንክ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በባሌ ዞን በሮቤ ከተማ ያስገነባውን ባለ 4 ወለል ዘመናዊ ሕንጻ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሀላፊዎች በተገኙበት በድምቀት በማስመረቅ ለአገልግሎት አብቅቷል፡፡
የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ባላቸው የቱሪስት መስህቦችና በምርታማነቱ በሚታወቀው የባሌ ዞን መዲና በሆነችው የሮቤ ከተማ የተገነባው ይህ ህንጻ የተገነባበት አካባቢ ለንግድና ለተለያዩ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች ተፈላጊ ሥፍራ በመሆኑ ለሀገሪቱ ብሎም ለክልሉ ያለው የኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

Nov 28, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
55.6854 56.7991
GBP
67.1870 68.5307
EUR
60.9588 62.1780
AED
13.7216 13.9960
SAR
13.4363 13.7050
CHF
60.3764 61.5839

Exchange Rate
Close