አዋሽ ባንክ የመጀመርያው ግማሽ  ዓመት የስራ አፈፃፀም ግምገማ  አካሄደ።

አዋሽ ባንክ  እ.ኤ.አ. የ2022/23 በጀት አመት የመጀመርያው ግማሽ አመት የስራ አፍፃፀም ግምገማ  ጥር 28 ቀን 2015 ዓ.ም   ስካይላይት ሆቴል አካሂዷል። የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ፀሐይ ሽፈራው ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ያለፉት ስድስት ወራት  አጠቃላይ የባንኩ የስራ አፈጻጸም ከዕቅዱ አንፃር ሲታይ በሁሉም መለኪያዎች አበረታች መሆኑን ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱ የመጀመርያው ግማሽ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ቅርንጫፎችና ቀጠና ጽ/ ቤቶች የእውቅናና የማበረታቻ ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን  ጠንካራ አፈጻጸሙን ለማስቀጠል በአፈፃፀም ላይ  የተስተዋለሉ ክፍተቶችን በማሻሻል ባንኩን በኢንዱስትሪው ውስጥ ባለው መሪነት ለማስቀጠልም ከምግባባት ተደርሷል፡፡

በመጨረሻም የአዋሽ ባንክ ዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አምባሳደር ዶክተር ዲባባ አብደታ ባሰተላለፉት መልዕክት የባንኩ የስራ አመራሮችና አጠቃላይ ሰራተኞች  በአዲሱ ስትራቴጂ ላይ የተቀመጠውን የባንኩን  ራዕይ ማለትም እ.አ.አ በ2027 ከሶስት የምስራቅ አፍሪካ ምርጥ ባንኮች አንዱ እና እ.አ.አ በ2030 ከአፍሪካ 10 ምርጥ  ባንኮች መካከል አንዱ መሆን የሚለዉን ለማሳካት ስራቸውን በብቃትና በጥበብ እንዲሰሩ  አሳስበዋል።

May 02, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.9239 58.0624
GBP
68.1921 69.5559
EUR
61.0167 62.2370
AED
14.0245 14.3050
SAR
13.7344 14.0091
CHF
59.5882 60.7800

Exchange Rate
Close