አዋሽ ባንክ የመጀመርያው ግማሽ  ዓመት የስራ አፈፃፀም ግምገማ  አካሄደ።

አዋሽ ባንክ  እ.ኤ.አ. የ2022/23 በጀት አመት የመጀመርያው ግማሽ አመት የስራ አፍፃፀም ግምገማ  ጥር 28 ቀን 2015 ዓ.ም   ስካይላይት ሆቴል አካሂዷል። የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ፀሐይ ሽፈራው ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ያለፉት ስድስት ወራት  አጠቃላይ የባንኩ የስራ አፈጻጸም ከዕቅዱ አንፃር ሲታይ በሁሉም መለኪያዎች አበረታች መሆኑን ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱ የመጀመርያው ግማሽ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ቅርንጫፎችና ቀጠና ጽ/ ቤቶች የእውቅናና የማበረታቻ ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን  ጠንካራ አፈጻጸሙን ለማስቀጠል በአፈፃፀም ላይ  የተስተዋለሉ ክፍተቶችን በማሻሻል ባንኩን በኢንዱስትሪው ውስጥ ባለው መሪነት ለማስቀጠልም ከምግባባት ተደርሷል፡፡

በመጨረሻም የአዋሽ ባንክ ዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አምባሳደር ዶክተር ዲባባ አብደታ ባሰተላለፉት መልዕክት የባንኩ የስራ አመራሮችና አጠቃላይ ሰራተኞች  በአዲሱ ስትራቴጂ ላይ የተቀመጠውን የባንኩን  ራዕይ ማለትም እ.አ.አ በ2027 ከሶስት የምስራቅ አፍሪካ ምርጥ ባንኮች አንዱ እና እ.አ.አ በ2030 ከአፍሪካ 10 ምርጥ  ባንኮች መካከል አንዱ መሆን የሚለዉን ለማሳካት ስራቸውን በብቃትና በጥበብ እንዲሰሩ  አሳስበዋል።

Nov 28, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
55.6854 56.7991
GBP
67.1870 68.5307
EUR
60.9588 62.1780
AED
13.7216 13.9960
SAR
13.4363 13.7050
CHF
60.3764 61.5839

Exchange Rate
Close