አዋሽ ባንክ የመጀመርያው ግማሽ  ዓመት የስራ አፈፃፀም ግምገማ  አካሄደ።

አዋሽ ባንክ  እ.ኤ.አ. የ2022/23 በጀት አመት የመጀመርያው ግማሽ አመት የስራ አፍፃፀም ግምገማ  ጥር 28 ቀን 2015 ዓ.ም   ስካይላይት ሆቴል አካሂዷል። የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ፀሐይ ሽፈራው ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ያለፉት ስድስት ወራት  አጠቃላይ የባንኩ የስራ አፈጻጸም ከዕቅዱ አንፃር ሲታይ በሁሉም መለኪያዎች አበረታች መሆኑን ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱ የመጀመርያው ግማሽ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ቅርንጫፎችና ቀጠና ጽ/ ቤቶች የእውቅናና የማበረታቻ ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን  ጠንካራ አፈጻጸሙን ለማስቀጠል በአፈፃፀም ላይ  የተስተዋለሉ ክፍተቶችን በማሻሻል ባንኩን በኢንዱስትሪው ውስጥ ባለው መሪነት ለማስቀጠልም ከምግባባት ተደርሷል፡፡

በመጨረሻም የአዋሽ ባንክ ዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አምባሳደር ዶክተር ዲባባ አብደታ ባሰተላለፉት መልዕክት የባንኩ የስራ አመራሮችና አጠቃላይ ሰራተኞች  በአዲሱ ስትራቴጂ ላይ የተቀመጠውን የባንኩን  ራዕይ ማለትም እ.አ.አ በ2027 ከሶስት የምስራቅ አፍሪካ ምርጥ ባንኮች አንዱ እና እ.አ.አ በ2030 ከአፍሪካ 10 ምርጥ  ባንኮች መካከል አንዱ መሆን የሚለዉን ለማሳካት ስራቸውን በብቃትና በጥበብ እንዲሰሩ  አሳስበዋል።

Jul 26, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
57.4895 58.6393
GBP
70.6759 72.0894
EUR
62.3359 63.5826
AED
14.1646 14.4479
SAR
13.8682 14.1456
CHF
62.5028 63.7529

Exchange Rate
Close