አዋሽ ባንክ የመጀመርያው ግማሽ  ዓመት የስራ አፈፃፀም ግምገማ  አካሄደ።

አዋሽ ባንክ  እ.ኤ.አ. የ2022/23 በጀት አመት የመጀመርያው ግማሽ አመት የስራ አፍፃፀም ግምገማ  ጥር 28 ቀን 2015 ዓ.ም   ስካይላይት ሆቴል አካሂዷል። የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ፀሐይ ሽፈራው ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ያለፉት ስድስት ወራት  አጠቃላይ የባንኩ የስራ አፈጻጸም ከዕቅዱ አንፃር ሲታይ በሁሉም መለኪያዎች አበረታች መሆኑን ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱ የመጀመርያው ግማሽ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ቅርንጫፎችና ቀጠና ጽ/ ቤቶች የእውቅናና የማበረታቻ ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን  ጠንካራ አፈጻጸሙን ለማስቀጠል በአፈፃፀም ላይ  የተስተዋለሉ ክፍተቶችን በማሻሻል ባንኩን በኢንዱስትሪው ውስጥ ባለው መሪነት ለማስቀጠልም ከምግባባት ተደርሷል፡፡

በመጨረሻም የአዋሽ ባንክ ዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አምባሳደር ዶክተር ዲባባ አብደታ ባሰተላለፉት መልዕክት የባንኩ የስራ አመራሮችና አጠቃላይ ሰራተኞች  በአዲሱ ስትራቴጂ ላይ የተቀመጠውን የባንኩን  ራዕይ ማለትም እ.አ.አ በ2027 ከሶስት የምስራቅ አፍሪካ ምርጥ ባንኮች አንዱ እና እ.አ.አ በ2030 ከአፍሪካ 10 ምርጥ  ባንኮች መካከል አንዱ መሆን የሚለዉን ለማሳካት ስራቸውን በብቃትና በጥበብ እንዲሰሩ  አሳስበዋል።

Oct 18, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
119.0155 121.3958
GBP
146.3141 149.2403
EUR
129.0483 131.6293
AED
29.3241 29.9105
SAR
28.7101 29.2843
CHF
129.3940 131.9819

Exchange Rate
Close