አዋሽ ባንክ በቦረና ዞን በድርቅ ለተጎዱ ዜጎች 30 ሚሊዮን ብር ለገሰ

በተለያዩ የአገራችን ክፍሎች በተፈጥሯዊና ሰዉ ሰራሽ ችግሮች ሳቢያ ለተለያዩ ጉዳቶች ለሚጋለጡ ዜጎች ድጋፍ በማድረግ የሚታወቀዉ አዋሽ ባንክ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ቦረና ዞን በድርቅ ለተጎዱ ዜጎች የሰላሳ ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል።
አዋሽ ባንክ ባለፈዉ ዓመትም በቦረና ጉጂ ዞኖች በድርቅ ለተጎዱ ወገኖችና የብር 60 ሚሊዮን ብር ለግሷል።
በተመሳሳይ ሁኔታ በማህበራዊ ኃላፊነት መወጫ መርሐግብሩ በምዕራብ ኦሮሚያ ተከስቶ በነበረዉ የእርስ በርስ ግጭት ተፈናቅለዉ ለነበሩ ዜጎችና በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ንፋስ ቀላቅሎ በጣለዉ ከባድ ዝናብ ቤት ለፈረሰባቸዉ አባወራዎችም የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉ ይታወሳል።

Nov 28, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
55.6854 56.7991
GBP
67.1870 68.5307
EUR
60.9588 62.1780
AED
13.7216 13.9960
SAR
13.4363 13.7050
CHF
60.3764 61.5839

Exchange Rate
Close