አዋሽ ባንክ በአምቦ ከተማ አዲስ ህንፃ ሊገነባ ነው

በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የክልል ከተሞች የራሱን ህንፃ በመገንባት የሚታወቀው አዋሽ ባንክ በአምቦ ከተማ ከምድር በታች ቤዝመንት ያለው ባለ ሰባት ወለል (G+7) አዲስ ዘመናዊ ህንፃ ለመገንባት መሳይ ኦሊ ከተሰኘና በግንባታ ዘርፍ ከፍተኛ ልምድ ካለው የህንጻ ተቋራጭ ድርጅት ጋር የውል ስምምነት ተፈራርሟል፡፡
ለአምቦ ከተማ የመልካም ገፅታ ግንባታ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው የሚታመነው አዲሱ የአዋሽ ባንክ አምቦ ቅርንጫፍ ህንፃ ግንባታም በፍጥነት እንደሚጀመርና በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚውል የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው በፊርማ ሥነ ስነስርዓቱ ላይ ተናግረዋል፡፡

Sep 07, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
115.1001 118.7426
GBP
141.5006 145.9786
EUR
124.8029 128.7525
AED
28.3594 29.2569
SAR
27.7656 28.6444
CHF
125.1372 129.0973

Exchange Rate
Close