አዋሽ ባንክ በአምቦ ከተማ አዲስ ህንፃ ሊገነባ ነው

በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የክልል ከተሞች የራሱን ህንፃ በመገንባት የሚታወቀው አዋሽ ባንክ በአምቦ ከተማ ከምድር በታች ቤዝመንት ያለው ባለ ሰባት ወለል (G+7) አዲስ ዘመናዊ ህንፃ ለመገንባት መሳይ ኦሊ ከተሰኘና በግንባታ ዘርፍ ከፍተኛ ልምድ ካለው የህንጻ ተቋራጭ ድርጅት ጋር የውል ስምምነት ተፈራርሟል፡፡
ለአምቦ ከተማ የመልካም ገፅታ ግንባታ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው የሚታመነው አዲሱ የአዋሽ ባንክ አምቦ ቅርንጫፍ ህንፃ ግንባታም በፍጥነት እንደሚጀመርና በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚውል የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው በፊርማ ሥነ ስነስርዓቱ ላይ ተናግረዋል፡፡

May 13, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.9632 58.1025
GBP
68.2066 69.5707
EUR
61.4063 62.6344
AED
14.0337 14.3144
SAR
13.7450 14.0199
CHF
60.0241 61.2246

Exchange Rate
Close