የQAXALEEWWAN (ቀጠሌዋን) የስራ ፈጠራ ውድድር አሸናፊዎች ሽልማታቸውን ተረከቡ

ለተከታታይ ሳምንታት በOBN ቴሌቪዥን በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ሰፊ የስርጭት ሽፋን በነበረውና QAXALEEWWAN (ቀጠሌዋን) በተሰኘው የስራ ፈጠራ ውድድር ላይ በመሳተፍ አሸናፊ ለሆኑ ተወዳዳሪዎች በዳኞች ውሳኔ መሰረት ከ 1 – 6ኛ ደረጃዎች ውስጥ ለገቡ አሸናፊዎች ለእያንዳንዳቸው ማለትም ለ1ኛ ደረጃ አሸናፊ የብር 1 ሚሊዮን፣ 2ኛ ለወጣው አሸናፊ የብር 700 ሺህ፣ ለ3ኛ የብር 500 ሺህ፣ ለ4ኛ የብር 300 ሺህ ፣5ኛ ደረጃ ላይ ለሚገኘው ተወዳዳሪ የብር 200 ሺህ እንዲሁም 6ኛ ለወጣው ብር 100 ሺህ የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል እንዲሁም ከዋስትና ነፃ እስከ ብር 5 ሚሊዮን ብድር እንደየ ፕሮጀክታቸው ሁኔታ ተመቻችቶላቸዋል ፡፡
ባንኩ በዛሬው እለት በስካይ ላይት ሆቴል ባካሄደው የመርሐ ግብሩ የማጠቃለያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት የአዋሽ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እንደገለፁት የኮርፖሬት ማህበራዊ ሃላፊነት አካል የሆነው ስራ ፈጣሪዎችን የሚያበረታታው ይህ ፕሮጀክት ለወደፊቱም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅሰዋል፡፡ በሥነ ሥርዓቱ ላይ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎችን ጨምሮ በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

Jul 26, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
57.4895 58.6393
GBP
70.6759 72.0894
EUR
62.3359 63.5826
AED
14.1646 14.4479
SAR
13.8682 14.1456
CHF
62.5028 63.7529

Exchange Rate
Close