የQAXALEEWWAN (ቀጠሌዋን) የስራ ፈጠራ ውድድር አሸናፊዎች ሽልማታቸውን ተረከቡ

ለተከታታይ ሳምንታት በOBN ቴሌቪዥን በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ሰፊ የስርጭት ሽፋን በነበረውና QAXALEEWWAN (ቀጠሌዋን) በተሰኘው የስራ ፈጠራ ውድድር ላይ በመሳተፍ አሸናፊ ለሆኑ ተወዳዳሪዎች በዳኞች ውሳኔ መሰረት ከ 1 – 6ኛ ደረጃዎች ውስጥ ለገቡ አሸናፊዎች ለእያንዳንዳቸው ማለትም ለ1ኛ ደረጃ አሸናፊ የብር 1 ሚሊዮን፣ 2ኛ ለወጣው አሸናፊ የብር 700 ሺህ፣ ለ3ኛ የብር 500 ሺህ፣ ለ4ኛ የብር 300 ሺህ ፣5ኛ ደረጃ ላይ ለሚገኘው ተወዳዳሪ የብር 200 ሺህ እንዲሁም 6ኛ ለወጣው ብር 100 ሺህ የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል እንዲሁም ከዋስትና ነፃ እስከ ብር 5 ሚሊዮን ብድር እንደየ ፕሮጀክታቸው ሁኔታ ተመቻችቶላቸዋል ፡፡
ባንኩ በዛሬው እለት በስካይ ላይት ሆቴል ባካሄደው የመርሐ ግብሩ የማጠቃለያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት የአዋሽ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እንደገለፁት የኮርፖሬት ማህበራዊ ሃላፊነት አካል የሆነው ስራ ፈጣሪዎችን የሚያበረታታው ይህ ፕሮጀክት ለወደፊቱም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅሰዋል፡፡ በሥነ ሥርዓቱ ላይ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎችን ጨምሮ በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

Oct 25, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
119.2055 121.5896
GBP
146.5477 149.4786
EUR
129.2543 131.8394
AED
29.3709 29.9583
SAR
28.7559 29.3311
CHF
129.6006 132.1926

Exchange Rate
Close