አዋሽ ባንክ በአምቦ ከተማ አዲስ ህንፃ ሊገነባ ነው

በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የክልል ከተሞች የራሱን ህንፃ በመገንባት የሚታወቀው አዋሽ ባንክ በአምቦ ከተማ ከምድር በታች ቤዝመንት ያለው ባለ ሰባት ወለል (G+7) አዲስ ዘመናዊ ህንፃ ለመገንባት መሳይ ኦሊ ከተሰኘና በግንባታ ዘርፍ ከፍተኛ ልምድ ካለው የህንጻ ተቋራጭ ድርጅት ጋር የውል ስምምነት ተፈራርሟል፡፡
ለአምቦ ከተማ የመልካም ገፅታ ግንባታ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው የሚታመነው አዲሱ የአዋሽ ባንክ አምቦ ቅርንጫፍ ህንፃ ግንባታም በፍጥነት እንደሚጀመርና በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚውል የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው በፊርማ ሥነ ስነስርዓቱ ላይ ተናግረዋል፡፡

Feb 12, 2025 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
124.9998 127.4998
GBP
153.3074 156.3735
EUR
135.5371 138.2478
JPY
0.7393 0.7541
SAR
30.0824 30.6841
AED
30.7258 31.3403
CAD
81.5563 83.1874
CHF
135.5787 138.2902
NOK
10.1355 10.3382
DKK
16.4011 16.7291