አዋሽ ባንክ “አዋሽ ለሁሉም” የተሰኘ ዲጂታል አነስተኛ የብድር አገልግሎት ይፋ አደረገ

ህዳር 24 ፣ 2016 ዓ.ም (አዲስ አበባ)፣ አዋሽ ባንክ “አዋሽ ለሁሉም” የተሰኘ አነስተኛ የብድር አገልግሎት የሚያገኙበት ዲጂታል የብድር አገልግሎት በዛሬው እለት የተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት አካላት እና እንግዶች በተገኙበት በኢሊሊ ሆቴል ይፋ አድርጓል።

በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፉና ዘመኑን የዋጁ የባንክ አገልግሎቶችን በመስጠት ተደራሽነቱን በማስፋት ላይ የሚገኘው አዋሽ ባንክ የደንበኞቹን ፍላጎት ለማርካት ደንበኞች ባሉበት ሆነው አነስተኛ የብድር አገልግሎት የሚያገኙበት “አዋሽ ለሁሉም” የተሰኘውን አገልግሎት እንዲሁም የሳኮስ አይቲ ሶሉዩሽን (SACCOs IT Solution) ቴክኖሎጂ ዛሬ ይፋ ሆኗል።

በሥነ-ስርዓቱ ላይ የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እንደገለፀት አዋሽ ባንክ በኢንዱስትሪው ውስጥ ያለውን የመሪነት ስፍራውን ይዞ እንዲቀጥልና የደንበኞቹን ፍላጎት ለማሟላት በየጊዜው አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ተግባራዊ እንደሚያደርግ አመላክተዋል፡፡

May 20, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.9985 58.1385
GBP
68.8367 70.2134
EUR
61.7864 63.0221
AED
14.0421 14.3229
SAR
13.7538 14.0289
CHF
59.8369 61.0336

Exchange Rate
Close