አዋሽ ባንክ አዲስ የፋይናንስ ቴክኖሎጂ ይፋ አደረገ

ነሐሴ 16/2015 (አዋሽ ባንክ) አዋሽ ባንክ እና አምሪፍ ኸልዝ ጋር በመተባበር በብድርና ቁጠባ ዘርፍ የበለፀገ አዲስ የፋይናንስ ቴክኖሎጂን ይፋ አድርጓል፡፡
“ሳኮስ ኮርፖሬት ቢዝነስ ሶልዩሽን” የተሰኘው ቴክኖሎጂ አነስተኛ እና መሰረታዊ የባንክ አገልግሎቶችን የሚሰጥ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ቴክኖሎጂው የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ሥራ ማህበራትን አገልግሎት ቀልጣፋ ለማድረግ፣ ተደራሽነታቸውን ለማጎልበት፣ ብሎም በዘርፉ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው የአዋሽ ባንክ ሲኒየር ቺፍ ሪቴይል ኤንድ ኤስ.ኤም.ኢ ባንኪንግ ኦፊሰር በአቶ ሄኖክ ተሰማ በሥነ ሥርዓቱ ላይ ገልጸዋል፡፡
ባንኩ ዛሬ ያስተዋወቀው የፋይናንስ ቴክኖሎጂ ለከፍታ የተቀናጀ የወጣቶች ፕሮጀክት የብድርና ቁጠባው ዘርፍ በነፃ ያቀረበ ሲሆን በዚህ አዲስ ቴክኖሎጂ የአባላት ምዝገባና አያያዝ፣ የብድር አገልግሎት አስተዳደር፣ አክሲዮን እና የአክሲዮን ድርሻ ክፍያን ጨምሮ ሌሎች በርካታ አገልግሎቶች ይሰጣል ተብሏል።

May 17, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.9888 58.1286
GBP
68.8685 70.2459
EUR
61.9126 63.1509
AED
14.0413 14.3221
SAR
13.7515 14.0265
CHF
60.2506 61.4556

Exchange Rate
Close