አዋሽ ባንክ አዲስ የፋይናንስ ቴክኖሎጂ ይፋ አደረገ

ነሐሴ 16/2015 (አዋሽ ባንክ) አዋሽ ባንክ እና አምሪፍ ኸልዝ ጋር በመተባበር በብድርና ቁጠባ ዘርፍ የበለፀገ አዲስ የፋይናንስ ቴክኖሎጂን ይፋ አድርጓል፡፡
“ሳኮስ ኮርፖሬት ቢዝነስ ሶልዩሽን” የተሰኘው ቴክኖሎጂ አነስተኛ እና መሰረታዊ የባንክ አገልግሎቶችን የሚሰጥ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ቴክኖሎጂው የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ሥራ ማህበራትን አገልግሎት ቀልጣፋ ለማድረግ፣ ተደራሽነታቸውን ለማጎልበት፣ ብሎም በዘርፉ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው የአዋሽ ባንክ ሲኒየር ቺፍ ሪቴይል ኤንድ ኤስ.ኤም.ኢ ባንኪንግ ኦፊሰር በአቶ ሄኖክ ተሰማ በሥነ ሥርዓቱ ላይ ገልጸዋል፡፡
ባንኩ ዛሬ ያስተዋወቀው የፋይናንስ ቴክኖሎጂ ለከፍታ የተቀናጀ የወጣቶች ፕሮጀክት የብድርና ቁጠባው ዘርፍ በነፃ ያቀረበ ሲሆን በዚህ አዲስ ቴክኖሎጂ የአባላት ምዝገባና አያያዝ፣ የብድር አገልግሎት አስተዳደር፣ አክሲዮን እና የአክሲዮን ድርሻ ክፍያን ጨምሮ ሌሎች በርካታ አገልግሎቶች ይሰጣል ተብሏል።

May 02, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.9239 58.0624
GBP
68.1921 69.5559
EUR
61.0167 62.2370
AED
14.0245 14.3050
SAR
13.7344 14.0091
CHF
59.5882 60.7800

Exchange Rate
Close