አዋሽ ባንክ የ2022/23 ዓመታዊ የሥራ አመራር ስብሰባ አካሄደ

አዋሽ ባንክ የ2022/23 ዓመታዊ የሥራ አመራር ስብሰባ ሐምሌ 28 እና 29 ቀን 2015 ዓ.ም በእስካይ ላይት ሆቴል አካሂዷል።

የአዋሽ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራዉ በጉባኤው የመክፈቻ ንግግር ላይ እንደ ገለፁት ባንኩ ባጠናቀቀዉ ሂሳብ ዓመት አመርቂ ውጤት ሊያስመዘግብ የቻለው ሊፍጠሩ የሚችሉ ተግዳሮቶችን ለመከላከል ያወጣውን እስትራቴጂ በአግባቡ በመከተልና በመተግበሩ ነው ብለዋል::

ባንኩ በተጠናቀቀዉ የሂሳብ ዓመት ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት የግል ባንኮች መካከል በሁሉም የባንኪንግ የስራ ዘርፎች የመሪነት ስፍራውን እንደያዘ የቀጠለ ሲሆን ይህንን ለማስቀጠል ባንኩ የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል ከፍተኛ መዋለ ንዋይ ፈሰስ በማድረግና ዘርፉን በሚደግፍ ቴክኖሎጂ በመታገዝ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ አክለዋል:: በመጨረሻም በተጠናቀቀዉ ሂሳብ ዓመት አመርቂ ውጤት ላስመዘገቡት ና የቀጠና ጽ/ቤቶች እና ቅርንጫፎች ዕውቅናና የማበረታቻ ሽልማት በማበርከት ስብሰባውን አጠናቋል::

May 17, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.9888 58.1286
GBP
68.8685 70.2459
EUR
61.9126 63.1509
AED
14.0413 14.3221
SAR
13.7515 14.0265
CHF
60.2506 61.4556

Exchange Rate
Close