አዋሽ ባንክ የ2022/23 ዓመታዊ የሥራ አመራር ስብሰባ አካሄደ

አዋሽ ባንክ የ2022/23 ዓመታዊ የሥራ አመራር ስብሰባ ሐምሌ 28 እና 29 ቀን 2015 ዓ.ም በእስካይ ላይት ሆቴል አካሂዷል።

የአዋሽ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራዉ በጉባኤው የመክፈቻ ንግግር ላይ እንደ ገለፁት ባንኩ ባጠናቀቀዉ ሂሳብ ዓመት አመርቂ ውጤት ሊያስመዘግብ የቻለው ሊፍጠሩ የሚችሉ ተግዳሮቶችን ለመከላከል ያወጣውን እስትራቴጂ በአግባቡ በመከተልና በመተግበሩ ነው ብለዋል::

ባንኩ በተጠናቀቀዉ የሂሳብ ዓመት ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት የግል ባንኮች መካከል በሁሉም የባንኪንግ የስራ ዘርፎች የመሪነት ስፍራውን እንደያዘ የቀጠለ ሲሆን ይህንን ለማስቀጠል ባንኩ የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል ከፍተኛ መዋለ ንዋይ ፈሰስ በማድረግና ዘርፉን በሚደግፍ ቴክኖሎጂ በመታገዝ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ አክለዋል:: በመጨረሻም በተጠናቀቀዉ ሂሳብ ዓመት አመርቂ ውጤት ላስመዘገቡት ና የቀጠና ጽ/ቤቶች እና ቅርንጫፎች ዕውቅናና የማበረታቻ ሽልማት በማበርከት ስብሰባውን አጠናቋል::

May 02, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.9239 58.0624
GBP
68.1921 69.5559
EUR
61.0167 62.2370
AED
14.0245 14.3050
SAR
13.7344 14.0091
CHF
59.5882 60.7800

Exchange Rate
Close