አዋሽ ባንክ የስራ እድል ፈጠራን የሚያበረታታ የ ‘ታታሪዎቹ’/ ቀጠሌዋን የሁለተኛ ዙር ፕሮጀክት ይፋ አደረገ

አዋሽ ባንክ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ከመወጣት አኳያ ስራ ፈጣሪዎችንና ወጣት ትውልድን ለማበረታታትና ተገቢውን የፋይናንስ ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችለውን ፕሮጀክት ቀርጾ ወደ ትግበራ መግባቱን ይፋ አድርጓል፡፡
በተካሄደው ሁለተኛው ዙር የ ‘ታታሪዎቹ’/ ቀጠሌዋን የስራ ፈጠራ ውድድር ማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት ላይ የባንኩ ዋና ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እንደገለፁት ስራ ፈጣሪ የሆኑ ዜጎቻችን በተለይም ወጣት ወንዶችና ሴት እህቶቻችን የእድሉ ተጠቃሚ በመሆን የቢዝነስ ሀሳባቸውን ዕውን በማድረግ በአገራቸው ዕድገት ላይ የራሳቸውን አሻራ እንዲያሳርፉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
የተወዳዳሪ ስራ ፈጣሪዎች ከጥቅምት 12 እስከ ህዳር 13 ቀን 2016 ዓ.ም በበይነ መረብ (ኦን ላይን) ወይንም በሁሉም አዋሽ ባንክ ቅርንጯፎች በአካል በመገኘት ማመልከት እንደሚችሉ ተጠቁሟል፡፡

May 02, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.9239 58.0624
GBP
68.1921 69.5559
EUR
61.0167 62.2370
AED
14.0245 14.3050
SAR
13.7344 14.0091
CHF
59.5882 60.7800

Exchange Rate
Close