አዋሽ ባንክ ዘመናዊ የዲጂታል ቅርንጫፎችን አገልግሎት አስጀመረ፡፡

አዋሽ ባንክ ጥቅምት 24 ፣ 2016 ዓ.ም (አዲስ አበባ)፣ ዘመናዊ እና አስተማማኝ የባንክ አገልግሎት ለደንበኞቹ ለማቅረብ ሁሌ የሚተጋው አዋሽ ባንክ የዲጂታል ቅርንጫፍ (e-Branch) የማስጀመሪያ መርሐ-ግብርን በአዲስ አበባ ጌቱ ኮሜርሻል ሴንተር እና ብስራተ ገብርኤል አካባቢ እንዲሁም ከአዲስ አበባ ውጪ በአዳማ ከተማ በይፋ በማስመርቅ አገልግሎት አስጀምሯል፡፡
ባንኩ ይፋ ያደረገው የዲጂታል ቅርንጫፎች ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ያሟሉ በመሆናቸው ደንበኞች ያለማንም ጣልቃ ገብነት በማንኛውም ጊዜ የሚፈልጉትን አገልግሎት እራሳቸውን በራሳቸው የማስተናገድ ዕድልን እንደሚፈጥር የባንኩ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው በስነ-ስርዓቱ ላይ ገልፀዋል፡፡

May 02, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.9239 58.0624
GBP
68.1921 69.5559
EUR
61.0167 62.2370
AED
14.0245 14.3050
SAR
13.7344 14.0091
CHF
59.5882 60.7800

Exchange Rate
Close