በስምምነቱ መሠረት የኤልክትሪክ ፍጆታ ክፍያ በአዋሽ ባንክ የክፍያ አማራጮች እንዲሳለጥ እና ሌሎችም የፋይናንስ ተቋማት ደንበኞች ያለ ምንም ውጣ ውረድ ክፍያቸውን ከሚፈልጉት የፋይናንስ ተቋም መክፈል እንዲችሉ የሚያደርግ መሆኑን ተጠቁሟል።
አዋሽ ባንክ አገልግሎቱን ይበልጥ ምቹና ቀልጣፋ ለማድረግ ዘመኑን የዋጁ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ግዥ በመፈፀም አዲስ የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎቶችን በማስፋፋት ላይ ሲሆን የደንበኞቹን አስተያየት፣ ጥያቄ እና ቅሬታ ከግምት ውስጥ በማስገባት በየጊዜው የአሰራር ሂደቶቹን እያሻሻለ የደንበኞቹን ፍላጐት በማርካት ታላቅ አመኔታን እያተረፈ መሆኑን የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው በፊርማው ሥነ ሥርዓት ላይ ገልጸዋል፡፡