አዋሽ ባንክ እና አዋሽ ኢንሹራንስ ኩባንያ አረንገጓዴ አሻራቸውን አኖሩ

የእህት ኩባንያዎቹ አዋሽ ባንክ እና አዋሽ ኢንሹራንስ ሠራተኞች በዛሬው እለት ሐምሌ 01 ቀን 2015 ዓ.ም ለአምስተኛው ዙር የአረንጓዴ አሻራ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከቦሌ ክፍለ ከተማ የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በአይሲቲ ፓርክ 20 ሺህ ችግኞችን በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል፡፡

እህት ኩባንያዎቹ በኮርፖሬት ማህበራዊ ኃላፊነት መርሐ ግብራቸው በስፋት ከሚሳተፉባቸው ተግባራት አንዱ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎችን መደገፍ ሲሆን በተለይ ባለፉት 29 ዓመታት ውስጥ በሀገራችን የልማትና የምጣኔ ሀብት ዕድገት ውስጥ አሻራቸውን ካስቀመጡት የግል የፋይናንስ ተቋማት መካከል ግንባር ቀደም መሆናቸው ይታወቃል፡፡

May 02, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.9239 58.0624
GBP
68.1921 69.5559
EUR
61.0167 62.2370
AED
14.0245 14.3050
SAR
13.7344 14.0091
CHF
59.5882 60.7800

Exchange Rate
Close