አዋሽ ባንክ አዲስ የፋይናንስ ቴክኖሎጂ ይፋ አደረገ

ነሐሴ 16/2015 (አዋሽ ባንክ) አዋሽ ባንክ እና አምሪፍ ኸልዝ ጋር በመተባበር በብድርና ቁጠባ ዘርፍ የበለፀገ አዲስ የፋይናንስ ቴክኖሎጂን ይፋ አድርጓል፡፡
“ሳኮስ ኮርፖሬት ቢዝነስ ሶልዩሽን” የተሰኘው ቴክኖሎጂ አነስተኛ እና መሰረታዊ የባንክ አገልግሎቶችን የሚሰጥ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ቴክኖሎጂው የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ሥራ ማህበራትን አገልግሎት ቀልጣፋ ለማድረግ፣ ተደራሽነታቸውን ለማጎልበት፣ ብሎም በዘርፉ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው የአዋሽ ባንክ ሲኒየር ቺፍ ሪቴይል ኤንድ ኤስ.ኤም.ኢ ባንኪንግ ኦፊሰር በአቶ ሄኖክ ተሰማ በሥነ ሥርዓቱ ላይ ገልጸዋል፡፡
ባንኩ ዛሬ ያስተዋወቀው የፋይናንስ ቴክኖሎጂ ለከፍታ የተቀናጀ የወጣቶች ፕሮጀክት የብድርና ቁጠባው ዘርፍ በነፃ ያቀረበ ሲሆን በዚህ አዲስ ቴክኖሎጂ የአባላት ምዝገባና አያያዝ፣ የብድር አገልግሎት አስተዳደር፣ አክሲዮን እና የአክሲዮን ድርሻ ክፍያን ጨምሮ ሌሎች በርካታ አገልግሎቶች ይሰጣል ተብሏል።

Feb 04, 2025 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
124.7041 127.1982
GBP
153.3074 156.3735
EUR
135.2163 137.9206
JPY
0.7393 0.7541
SAR
30.0824 30.6840
AED
30.7258 31.3403
CAD
81.5563 83.1874
CHF
135.5787 138.2903
NOK
10.1355 10.3382
DKK
16.4011 16.7291